ውክፔዲያ
amwiki
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8B%E1%8A%93%E1%8B%8D_%E1%8C%88%E1%8C%BD
MediaWiki 1.39.0-wmf.21
first-letter
ፋይል
ልዩ
ውይይት
አባል
አባል ውይይት
ውክፔዲያ
ውክፔዲያ ውይይት
ስዕል
ስዕል ውይይት
መልዕክት
መልዕክት ውይይት
መለጠፊያ
መለጠፊያ ውይይት
እርዳታ
እርዳታ ውይይት
መደብ
መደብ ውይይት
በር
በር ውይይት
TimedText
TimedText talk
Module
Module talk
Gadget
Gadget talk
Gadget definition
Gadget definition talk
ውይይት:ኢትዮጵያ
1
2016
372121
367185
2022-07-23T06:47:45Z
31.208.224.251
/* Question about geographical names */ Reply
wikitext
text/x-wiki
== Question about geographical names ==
Can anyone translate to Amharic geographical names listed below? [[አባል:Aotearoa|Aotearoa]] 15:53, 2 ኖቬምበር 2009 (UTC)
*Somali Peninsula -
*Ethiopian Highlands - የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች
*Somali highlands - የሶማሌ (for the Ethiopian region, for the country Somalia የሶማሊያ) ከፍተኛ ቦታዎች
*Danakil Desert - ደንከል በርሃ
*Ethiopian Rift Valley (Abyssinian Rift Valley) የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ (የአቢሲኒያ ስምጥ ሸለቆ)
Thank you. [[አባል:Aotearoa|Aotearoa]] 15:15, 7 ኖቬምበር 2009 (UTC)
:Somali Peninsula = የሶማሌ ባሕረ-ሰላጤ, which is the same as The Horn of Africa = የአፍሪካ ቀንድ። [[ልዩ:Contributions/31.208.224.251|31.208.224.251]] 06:47, 23 ጁላይ 2022 (UTC)
99o5x1bwxtufzt6ez4ewjert2oyoyt4
ስቅለት (የማይክል አንጄሎ ቅርጽ)
0
13943
372119
372107
2022-07-22T20:01:13Z
Amarigna
40141
typos
wikitext
text/x-wiki
[[File:Pietro Perugino 040.jpg|250px|thumb|ስቅለት]]
[[File:Santo Spirito, sagrestia, crocifisso di michelangelo 04.JPG|142px|thumb|Right|
“የማይክል አንጀሎ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉስ”]]
ስቅለት በማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ
በ1492 ስቅለት የተባለውን ቅርጽ ከእንጨት በመቅረጽ የእንደገና መወለድ ዘመን ሰአሊ ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ በስጦታ አበርክቷል። ስቅለት የተባለው ቅርጽ አሁን የሚገኘው ቅድስት ማሪያም ዴላ ሳንቶ ስፒሪቶ ከሚባለው ቤተክርስቲያን ውስጥ ከመንበሩ በላይ ነው። ቅርጹ ብዙ ትኩረትን የሳበው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እርቃነ ስጋውን በመሆኑ ነው::
== ታሪኩ ==
ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ በቅድስት ማሪያም ሳንቶ ስፒሪቶ ቤተክርስቲያን (ፍሎሬንዝ) ስብሰባ ውስጥ በእንግዳነት ተጋብዞ ነበር እድሜውም አስራ ሰባት አመት ነበር። ከሎሬንዞ ደ ሚዲቺ ሞት በኋላ በዚህም የሰውነት ቅርጽን ትምህርቱን በሞቱ ሰዎች አስከሬን ላይ ልምምድ አድርጓል። ይህንንም ልምምድ ያደረገው በቤተ ክርስቲያኑ ንብረት ከነበረው ሆስፒታል ውስጥ ነበር። በአንጻሩም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት ከ እንጨት በመቅረጽ ለቤተ ክርስቲያኑ በስጦታ አበረከተ። ይህም ቅርጽ ዛሬ በቅድስት ማሪያም ሳንቶ ስፒሪቶ ቤተክርስቲያን ከመንበሩ በላይ ይገኛል።
== መግለጫ ==
ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እርቃነ ስጋውን የቀርጸው ምንም ሳይጋነን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንደሚለው የሮማን ወታደሮች ልብሱን ይከፋፈሉታል በእጀ ጠባቡንም እጣ ይጣጣሉበታል ብሎ የተጻፈው እንዲፈጽም ነው። መዝሙር 22፡18 በወንጌሎቹም ሁሉ ላይ ይህ ተጽፏል። ፓውሎስ ግን በዝርዝር ጽፎታል።
“ወታደሮቹ ኢየሱስን ከስቀሉ በኋላ እጀ ጠባቡ ሲቀር ልብሱን ወስደው ለእያንዳንዱ አንድ አንድ እንዲዳረስ ለአራት ተከፋፈሉት እጀ ጠባቡንም ከላይ አንድ ወጥ ሆኖ ያለ ስፌት የተሰራ ነበር። ስለዚህ ዕጣ ተጣጥለን ለሚደርሰው ይድረስ እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም የሆነው ልብሴን ተከፋፈሉት በእጀ ጠባቤም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ የሚለው የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ነው። ወታደሮቹ ያደረጉትም ይህንኑ ነው። “
ይህን የስቅለት ቅርጽ ልዩ የሚያደርገው ከመስቀሉ ላይ ያለው የጌታችን የመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክስ በ ዕብራይስጥ በግሪክ እና በላቲን ቋንቋ የተጻፈ ነበር። ቃሉም የሚለው ” የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉስ” የሚል ነበር። ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲም ይህን ጽሁፍ የወሰደው ከዮሐንስ ወንጌል ምእራፍ 19 19ነው። ጲላጦስም ጽሑፍ ጽፎ በመስቀሉ ላይ አንጠለጠለው። ጽሑፉም “የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉስ” የሚል ነበር ። የአይሁድ የካህናት አለቆች ጲላጦስን በመቃወም እርሱ “የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ ጻፍ እንጂ “የአይሁድ ንጉስ ብለህ አትጻፍ አሉት ጲላጦስም በቃ የጻፍኩትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ።
ከወታደሮቹ አንዱ ኢየሱስን በጦር ወጋው ወዲያውም ደምና ዉሃ ፈሰሰ ይህን ያየው ሰው ምስክርነቱን ሰጥቶአል ምስክርነቱም እውነት ነው እውነት እንደሚናገርም ያውቃል እናንተም እንድታምኑ ይመሰክራል። ይህም የሆነው መጽሐፍ ከአጥንቴ አንድም አይሰበርም ያለው እንዲፈጸም ሌላውም መጽሐፍ የወጉትም ያዩታል ስለሚል ነው።
ከቀኑ ስድስት ስዓት ያህል ነበር እስከ ዘጠኝ ሰአት ድረስም በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ የፀሓይ ብርሃን ተከልክሎአልና። የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ተቀዶ ለሁለት ተከፈል። ኢየሱስም ድምጹን ከፍ አድርጎ “ኤሎሄ!ኤሎሄ!ላማ ሰበቅታኒ?” እያለ ጮኸ ትርጉሙም “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?” ማለት ነው።
ኢየሱስም በታላቅ ድምጽ ጮኸ አባት ሆይ መንፈሴን በእጅህ እሰጣለሁ አለ ይህንንም ብሎ ሞተ።
በእንደገና መወለድ አርቲስት ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ የተሰራው ይህ የጌታችን መድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት መሰረት ያደረገው መጽሐፍ ቅዱሱን ነው።
አሁን የአለም የፍርድ ቀን ነው ። የአለም ንጉስ መከራን ይቀበላል። እኔ ከሞት እነሳለሁ ለአለም ሕዝብ ሁሉ ንስሓና የኅጢአት ስርየት በስሜ ይሰበካል።
== ይህን ይመልከቱ ==
የማይክል አንጄሎ ስራዎች በከፊል
[[መደብ:ሥዕል]]
quaetdjwzurh2ms7geer4f2az8yfldw
ወንጌል
0
14392
372120
353323
2022-07-22T20:04:33Z
Amarigna
40141
/* growthexperiments-addlink-summary-summary:3|0|0 */
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#8FBC8F|above=ወንጌል|image=[[File:DSC 0156 - Biblia etíope na catedral de Axum.JPG|thumb|center|ከ፩ሺ ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው መጽሐፍ ቅዱስ]]
|caption=|headerstyle=background:#8FBC8F|header1= የመዳኛ መልዕክት|headerstyle=background:#8FBC8F|header8=<span style="color:#77B5FE">
</span>|label1=|data1=|label2=ዋና ፀሐፊዎች|data2=[[የማርቆስ ወንጌል|ቅዱስ ማርቆስ]]<br>[[የሉቃስ ወንጌል|ቅዱስ ሉቃስ]]<br>[[የዮሐንስ ወንጌል|ቅዱስ ዮሐንስና]]<br>[[የማቴዎስ ወንጌል|ቅዱስ ማቴዎስ]] |label3=የወንጌል ሌላ ስሙ|data3='''[[አዲስ ኪዳን]]''' |label4=|data4=|label5=|data5=|captionstyle=|header5=}}
ወንጌል የሚለው ቃል (ከላቲን evangelium / ኢቫንጄሊየም, ይህም ራሱ ከጥንት የግሪክ ቃል εὐαγγέλιον / ኧውጄሊዮን = አስደሳች መልዕክት) ከሚለው የተገኘ ቃል ነው። ወንጌል ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነ መልካም የምሥራች ነው፡፡ የንስሐ፣ የመፍትሄ፣ የሰላም፣ የፍቅር፣ የተስፋ፣ የደኅንነት፣ የእርቅ፣ ከፍርድ የመዳን፣ የዘላለም ሕይወት፣ ትምህርት የሚገኝበት ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡
'''[[ኢየሱስ ክርስቶስ]]''' የእግዚአብሔር መንግስት አዋጅ የሆነውን ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ እሱ ራሱ እንደሰበከ [[መጽሐፍ ቅዱስ]] ይነግረናል (ማቴ.፬፡፳፫፣ ማርቆ.፩፡፲፬-፲፭)፡፡
የወንጌል ዋነኛው መልዕክት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የኃጢአት ሥርየት ነው። ሰዎች '''ከ[[እግዚአብሔር]]''' ቁጣ እንዲተርፉ፤ኃጢአት የሚያስከፍለውን ዋጋ ለመክፈል ማለት ከሁሉ የከፋውን ሞትን ለመሻር ክርስቶስ '''ከ[[ማርያም|ቅድስት ድንግል ማርያም]]''' በድንግልና ተወልዶ እንደ ሰው ሆኖ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ ከሞት መነሣቱን በፈቃደኝንት ማለትም በሰላማዊ መንገድ አምኖ ማሳመን ነው (ሐዋ.፲፫፡፳፰-፴፣፴፰። ሮሜ.፫፡፳፭-፳፮፣ 1ቆሮ.፲፭፡፫-፬)።
በተለይ የዘላለማዊ ሕይወት ዕጣዬ ምንዓይነት ነው ለሚለው ጥያቄ ወንጌል ግልፅ የሆነ መልስ ይሰጣል።
== የወንጌል ዋና መልእክት ==
የወንጌል አንኳር መልዕክት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የኃጢአት ሥርየት ነው። የድኅነት ሥራ በ'''[[ክርስቶስ]]''' ተፈፅሟል የአዋጁ ዋና መልዕክት ነው (ሐዋ.፪፡፴፰፣ ፭፡፴፩፣ ፲፡፵፫፣ ፲፫፡፴፰፣ ፳፮፡፲፰) ። የድኅነት ስራ በክርስቶስ ኢየሱስ ስለተከናወነ፣ ሰዎች በእርሱ እንዲያምኑ እና የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ የሚነገር የምስራች ነው። ሐዋርያው '''[[ጳውሎስ]]''' እንደተናገረው ወንጌል በመስቀል ላይ የተከናወነውን አስደናቂ የድኅነት ስራ የማወጅ ተግባር ነው፣ “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ..” (፩ኛቆሮ.፲፭፡፩-፬)። የክርስቶስ ሞት እና '''[[ትንሳዔ]]''' የወንጌል ማዕከል ነው። ወንጌል ለፍጥረት ሁሉ የሚታወጅ የመስቀሉ የማዳን ሥራ ነው፣ “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው…” (፩ኛ.ጢሞ.፩፡፲፭)። ወንጌል ሰዎች ከኃጢአታቸው ንስሃ በመግባት የበደላቸውን ስርየት እንዲቀበሉ ይናገራል፣ “..በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከ'''[[ኢየሩሳሌም]]''' ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል” (ሉቃ.፳፬፡፵፯) ።
== በወንጌል የተገኘው ደኅንነት ==
የሰው ልጅ በመስቀል ላይ በተሰራው የድኅነት ሥራ በማመን
<blockquote>
*የኃጢአት ሥርየትን ያገኛል፣
*ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ይታረቃል፣
*እንደ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል፣
*የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ መንግስት ይወርሳል
*ከእግዚአብሔር ጋር ወደ ቀደመው የፍቅር ህብረት ይመለሳል
*በዚህ ዓለም ሲኖር የዘላለማዊ ተስፋ ያገኛል
*የምሥራቹን ወንጌል የማወጅ መብትና ብቃትን ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል
*በኃጢአት ምንክንያት ከሚመጣ የእግዚአብሔር ፍርድ ይድናል
</blockquote>
== ኢየሱስ ከሰበካቸው ==
“'''[[ኢየሱስ]]''' የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና ዘመኑ ተፈጸመ '''የ[[እግዚአብሔር]]ም''' መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ '''[[ገሊላ]]''' መጣ” (ማርቆ.፩፡፲፬-፲፭)። መጽሐፍ እንደሚል “በልጁ የሚያምን የዘላለም ህይወት አለው” (ዮሐ.፫፡፴፮)። በኃጢአት ምክንያት ከሚመጣ የዘላለምም ፍርድ ያመልጣል፣ “በእርሱ የሚያምን አይፈረድበትም..”(ዮሐ.፫፡፲፰)። ይሄንን የድኸነት ወንጌል ሐዋርያትም ሰብከውታል፣ “ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ '''የ[[መንፈስ ቅዱስ]]ንም''' ስጦታ ትቀበላላችሁ” (ሐዋ.፪፡፴፰)። የጥንት '''የ[[ቤተክርስቲያን]]''' አባቶችም ሰብከውታል።
== ወንጌል በእስልምና ==
“ወንጌል” የሚለው የግሪኩ ቃል “አንጀሊኦን” εὐαγγέλιον ሲሆን “የምስራች” አሊያም “መልካም ዜና” የሚል ፍቺ አለው፣ “ኢንጂል” إنجيل የሚለው የአረቢኛው ቃል “ኢወንጀሊየን” ܐܘܢܓܠܝܘܢ ከሚለው አረማይክ ቃል አቻ ሲሆን ትርጉሙ በተመሳሳይ “የምስራች” ማለት ነው፣ “ኢንጂል” የሚለው ቃል በቁርአን 12 ጊዜ ተጠቅሶ ይገኛል፤ ይህም ወንጌል ለኢሳ የተሰጠው ወህይ ነው፦
19:30 ሕፃኑም አለ እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ መጽሐፍም *”ሰጥቶኛል”* ነቢይም አድረጎኛል።
57:27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን የመርየምን ልጅ ኢሳንም አስከተልን፤ *”ኢንጅልንም ሰጠነው”*፤
5:46 *”ኢንጂልንም”* በውስጡ ቀጥታና ብርሃን ያለበት በስተፊቱ ያለችውን ተውራትንም የሚያረጋግጥ ለጥንቁቆችም መሪና ገሣጭ ሲሆን *”ሰጠነው”*።
ኢየሱስ ከራሱ ሳይሆን የላከው የሰጠውን ቃል እንደሚናገር እንጂ ከራሱ ምንም ሳይናገር ያ የተሰጠውን ቃል ለሃዋርያት እንደሳጣቸው ይናገራል፦
ዮሐንስ 12:49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ *”የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”*።
ዮሐንስ 17:8 *”የሰጠኸኝን ቃል”* ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥
ይህም የተሰጠው ቃል የላከው የፈጣሪ ንግግር ነው፦
ዮሐንስ 17:14 እኔ *”””ቃልህን””* ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው።”
ዮሐንስ 14:24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል *””””የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም”””*።
ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። *”ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም”*፤
ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያስተምር የነበረው ከፈጣሪ እየሰማ ነበር፦
ዮሐንስ 8.40 ነገር ግን አሁን *”ከእግዚአብሔር የሰማሁትን”* እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤
ዮሐንስ 8.26 ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም *”ከእርሱ የሰማሁትን”* ይህን ለዓለም እናገራለሁ አላቸው።
ዮሐንስ 5:30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ *”እንደ ሰማሁ”* እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።
ዮሐንስ 15:15 ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ *”ከአባቴ የሰማሁትን”* ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና።”
ዮሐንስ 12:50 ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች አውቃለሁ። ስለዚህ *”እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ”*።
እግዚአብሔር ኢየሱስ የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ ይህም ቃል የእግዚአብሔር ወንጌል ነው፤ ሕዝቡም የሚሰሙት የእግዚአብሔር ቃል ነበረ፦
ዮሐንስ 3፥34 እግዚአብሔር የላከው የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤
ሉቃስ5፥1 ሕዝቡም የእግዚአብሔርን ቃል እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ [[ባሕር-ዳር|ባሕር ዳር]] ቆሞ ነበር፤
“ነብይ” נָבִיא ማለት በዕብራይስጥ “ተናጋሪ” ወይም “ነጋሪ” ማለት ነው፤ ነብይ ማለት የሌላ ማንነት ንግግር ተቀብሎ የሚያስተላልፍ “አፈ-ቀላጤ” ወይም “ቃል አቀባይ” ማለት ነው፤ በዚህ ስሌት ኢየሱስ ከአምላክ ሰምቶ የሚያስተላልፍ ነብይ ነው፦
ዘኍልቍ 12:6 እርሱም። ቃሌን ስሙ፤ በመካከላችሁ *“ነቢይ”* ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር “በራእይ” እገለጥለታለሁ፥ ወይም “በሕልም” እናገረዋለሁ።
ማቴዎስ 21፥11 ሕዝቡም። ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ *”ነቢዩ ኢየሱስ ነው”* አሉ።”
ሉቃስ 24፥19 እርሱም። ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት። *በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ ነው”* ።
ማርቆስ 6፥4 ኢየሱስም። *ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው*።”
ታዲያ ከፈጣሪ ተሰጦት ሲያስተላልፍ የነበረው ቃል ምንድን ነው? ካልን ወንጌል ነው፤ ኢየሱስ ሲናገረው የነበረው ወንጌል እንደነበር ይናገራል፦
ሉቃ 4:17 የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች *ወንጌልን እሰብክ* ዘንድ ቀብቶኛልና፤
ሉቃ4:43 እርሱ ግን። ስለዚህ *ተልኬአለሁና ለሌሎቹ ከተማዎች ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እሰብክ ዘንድ ይገባኛል* አላቸው።
ማቴዎስ 4:23 ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ የመንግሥትንም *ወንጌል እየሰበከ* በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ በገሊላ ሁሉ ይዞር ነበር።
ማቴዎስ 9:35 ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው *እያስተማረ፥ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ*፥ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ፥ በከተማዎችና በመንደሮች ሁሉ ይዞር ነበር።
ማርቆስ 1:14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን *ወንጌል እየሰበከና*። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ *በወንጌልም እመኑ* እያለ ወደ ገሊላ መጣ።
ኢየሱስ *”በወንጌል እመኑ”* ያለው የማቴዎስን፣ የማርቆስን፣ የሉቃስን፣ እና የዮሐንስን ትረካ ሳይሆን ከአላህ እንዲናገር የተሰጠውን መልእክት ነው፤ ኢየሱስ ከፈጣሪው ተሰጦት ሲናገር የነበረውን ወንጌል እኛ ሙስሊሞች እናምንበታለን። ወንጌል የኢየሱስ ወንጌል ብቻ ነው፤ የኢየሱስ ወንጌል የሚጀምረው ማስተማር ከጀመረበት ጊዜ ነው፤ ማስተማር የጀመረው በሰላሳ አመቱ ነው፦
ማርቆስ 1፥1 *”የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ”*
ማርቆስ 1:14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን *ወንጌል እየሰበከና*። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ *በወንጌልም እመኑ* እያለ ወደ ገሊላ መጣ።
ሉቃስ 3:23 *”ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር”* ፤
ማስታወሻ፦ “ማርቆስ 1፥1 ላይ *የእግዚአብሔር ልጅ* የሚለው የግሪኩ ቀዳማይ እደ-ክታባት ላይ የለም”
ከማስተማሩ በፊት ስለ ውልደቱ እና ተልእኮውን ከጨረሰ በኃላ ስለ እርገቱ የሚያወሩት የአራቱ ወንጌላት ክፍሎች ወንጌል ሳይሆኑ በኢየሱስ ወንጌል ላይ የተጨመሩ *”የታሪክ መዝገብ”* ወይም “የትውልድ መጽሐፍ” ነው፦
ማቴዎስ 1፥1 የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ *”የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ”* ።
ሉቃ1:1-4 የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት *እንዳስተላለፉልን*፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር *”ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ”*፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው *”ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ”*።
አላህ ከእርሱ የወረውን ይህንን እውነት በሰው ትምህርት ቅጥፈት እንደቀላቀሉት ይናገራል፦
3:71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! *”እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ?”* እውንትም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ?
“እውነት” የተባለው ከአላህ የወረደው ቃሉ ነው፦
34:48 ፦ጌታዬ *“እውነትን ያወርዳል”*፤ ሩቅ የኾኑትን ሚስጢሮች ሁሉ ዐዋቂ ነው በላቸው።
“ውሸት” የተባለው ደግሞ መጽሐፉን በእጆቻቸው ፅፈው “ይህ ከአላህ ዘንድ ነው” ብለው የቀጠፉት ጭማሬ ነው፦
2:79 ለነዚያም *”መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በእርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው”*፡፡ ለእነርሱም ከዚያ *”እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው”*፡፡ ለእነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡
ስለዚህ ለኢየሱስ የተሰጠው የመጀመሪያው ወንጌል ከሰዎች ቃል ጋር ተበርዟል፤ ከላም የታለበ ወተት በብርጭቆ ተቀምጦ ሳለ በቡና ቢቀላቅሉት የመጀመሪያው ስረ-መሰረት ስለሌለ ሙሉ ወተት ሳይሆን ማኪያቶ ይባላል፤ ከላሟ የታለበው ወተት የት ገባ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው መልሳችሁ ተበርዟል ነው፤ ማክያቶ ውስጥ ወተት የለም እንዴ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? በቅሪት ደረጃ አለ፤ በተመሳሳይም ከአላህ ለኢየሱስ የተሰጠው ወንጌል ሳለ በሰው ቃል ቢቀላቅሉት የመጀመሪያው ስረ-መሰረት ስለሌለ ሙሉ ወንጌል ሳይሆን ብርዝ ይባላል፤ ከአላህ ለኢየሱስ የተሰጠው ወንጌል የት ገባ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? መልሳችሁ ተበርዟል ነው፤ የመጸሐፉ ሰዎች ውስጥ የወንጌል ቅሪት የለም እንዴ? ብትባሉ መልሳችሁ ምንድን ነው? በቅሪት ደረጃ አለ ነው፤ ያንን በቁርአን መዝነን እንቀበለዋለን፤ [[ቁርአን]] ያንን እነርሱ ጋር ያለውን መለኮታዊ ቅሪት ሊያረጋግጥ ወርዷል፦
4:47 እላንተ መጽሐፉ የተሰጣችሁ ሆይ! .. *”ከእናንተ ጋር ያለውን የሚያረጋግጥ”* ኾኖ ባወረድነው ቁርአን እመኑ፣
2:41 *”ከእናንተ ጋር ያለውን የሚያረጋግጥ”* ሆኖ ባወረድኩትም ቁርአን እመኑ፡፡
የመጽሐፉ ሰዎች ጋር ያሉት ቃላት ሙሉ ለሙሉ እውነትን ነው ብለን እንደማናምን ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ሐሰት ነው ብለን አናምንም፤ ቁርአን ከወረደበት ግብና አላማ፣ ፋይዳና ሚና አንዱ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነት ለማረጋገጥና ቀጥፈው የጨመሩትን ሐሰት ሊያርም ነው፤ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነትን ስለሚያረጋግጥ “ሙሰዲቃን” مُصَدِّقًا “አረጋጋጭ” ሲባል፤ የሰዎች ንግግሮች የገቡበትን በማረሙ ደግሞ “ሙሃይሚን” مُهَيْمِنًا “አራሚ” correcter” ወይም “ተቆጣጣሪ”supervisor” የሚል ስም አለው፦
5:48 ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ *”አረጋጋጭ”* እና በእርሱ ላይ *”ተጠባባቂ”* ሲሆን በእውነት አወረድን፤
ሰዎች በወንጌሉ ላይ መጨምራቸው ብቻ ሳይሆን በመደበቅ የቀነሱትም ነገር አለ፤ በ 397 AD የተደረገው የካርቴጅ ጉባኤ ብዙ የወንጌል ቅሪት አፓክራፋ ብሎ ቀንሷል፤ “አፓክራፋ” ማለት “አፓክራፎስ” ἀπόκρυφος ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን “ድብቅ” “ስውር” ማለት ነው፦
5፥15 የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! *”ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው”* ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ ከአላህ ዘንድ ብርሃንና ገላጭ መጽሐፍ በእርግጥ መጣላችሁ፡፡
2፥146 እነዚያ መጽሐፍን የሰጠናቸው ወንዶች ልጆቻቸውን እንደሚያውቁ ያውቁታል፡፡ ከእነሱም የተለዩ ክፍሎች እነርሱ የሚያወቁ ሲኾኑ *”እውነቱን በእርግጥ ይደብቃሉ”* ፡፡
ከተደበቁት ዋናው አጀንዳ የምስራቹን የምስራች ያሰኘው ኢየሱስ ስለ ነብያችን መምጣት ማብሰሩ ነው፤ አላህ ኢንጅል የሚለው ስለ ነብያችን መምጣት የሚተነብየውን ወንጌል እንደሆነ ቅቡልና እሙን ነው፦
61፥6 የመርየም ልጅ ዒሳም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና *”ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር”* ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ በግልጽ ተዓምራቶች በመጣቸውም ጊዜ «ይህ ግልጽ ድግምት ነው» አሉ፡፡
7፥157 ለእነዚያ ያንን እነርሱ ዘንድ *”በተውራትና በኢንጂል ተጽፎ የሚያገኙትን የማይጽፍና የማያነብ ነቢይ”* የኾነውን መልክተኛ የሚከተሉ ለኾኑት በእርግጥ እጽፍለታለሁ፡፡
2k6bt56ki6hozuwozn5e7yfhlh9thza
ማርያም
0
43708
372114
372058
2022-07-22T19:32:43Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#BCD4EC|above=ቅድስት ድንግል ማርያም<br>ንግሥተ ሰማይ ወምድር|image=[[ስዕል:እመብርሃን.png|259px|center|እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምስለ ፍቅርን አቅፋ]]|caption=|headerstyle=background:#BCD4EC|header1= እርግበ መንግሥተ ሰማያት።|header9=<span style="color:#"BCD4EC>
</span>
|label2=የተወለደችው|data2=15 ዓመት ከ[[ክርስቶስ]] ልደት በፊት|label3=የትውልድ ሀገር|data3=[[ሊባኖስ|እስራኤል፣ ይሁዳ ክፍለሀገር፣ በገሊላ አውራጃ፣ ናዝሬት በምትባል ስፍራ (አሁን ሊባኖስ ውስጥ ይገኛል)]] |label4=የምትከበረው|data4=[http://www.ethiopianorthodox.org/ በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን]<br>በ[[ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን]]<br>በ[[ኦርቶዶክስ]] ቤተክርስቲያኖችና<br>በአንዳንድ<br>ክርስቲያን ዲኖሚኔሽን ([[አንግሊካን]]፥ የጥንት ሉተ...)
|label5=የእናት ስም|data5=[[ሐና ወኢያቄም|ሐና]]|label6=የአባት ስም|data6=[[ሐና ወኢያቄም|እያቄም]]|label7= አንድዬ ልጅዋ|data7='''[[እየሱስ ክርስቶስ]]'''<br>[[File:ኢየሱስ ክርስቶስ.jpeg|68px|]]|label8=በዓላት|data8=፴፫ ሲሆኑ በየወሩ በ፳፩ ቀንና በተጨማሪ ዋና ዋናዎቹ፣<br>- የተወለደችበት ቀን [[ሐና ወኢያቄም|ልደታ]] [[ግንቦት ፩]]<br>- ለአይሁድ ቤተ መቅደስ የተሰጠችበት [[ሐና ወኢያቄም|ባአታ ማርያም]] [[ታኅሣሥ ፫]]<br>- ስደቷን ጨርሳ ወደ ትውልድ ሀገሯ የገባችበት [[ደብረ ፀሐይ ቍስቋም|ቁስቋም ማርያም]] [[ኅዳር ፮]]<br>- ቃል ኪዳን የተቀበለችበት [[ኪዳነ ምረት]] [[የካቲት ፲፮]]<br>- በጎሎጎታ እየተመላለሰች የጸለየችበት [[ጎልጎታ|ሰኔ ጎሎጎታ]] [[ሰኔ ፳፩]]<br>- ያረፈችበት ወይም የሞተችበት ቀን [[ጥር ፳፩]] [[አስትሮ ማርያም]] በ፷፬ ዓመቷ<br>- ዕርገቷና ትንሣኤዋ [[ፍልሠታ]] [[ነሐሴ ፲፮]]|data10=[[ስዕል:ውል ውል አለኝ ደጅሽ.webm|259px|center|thumb|ውል ውል አለኝ ደጅሽ
[[ውል ውል አለኝ ደጅሽ|''አድናቆት ለአኪልዳማ channel'']]]] |captionstyle=|header11=<span></span>}}
[[File:Ethiopia-Axum Cathedral-fresco-Black Madonna.JPG|thumb|160px| ማርያም ምስለ ፍቁርን ይዛ አክሱም ፅዮንማርያም የሚገኝ ስዕል]]
'''ድንግል ማርያም''' በ'''[[ክርስትና]]'''ና፣ በ[[እስልምና]] እምነቶች መሠረት የከበረችው የ'''[[ኢየሱስ ክርስቶስ]]''' እናት ነች።
በክርስትና እምነት የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ማለትም የወልድ እናት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ኃይል '''በ[[ሥላሴ]]''' ምርጫ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንደ ወለደችው ይታመናል ። በእግዚአብሔር ህሊና ከፍጥረት በፊት እንደነበረች ኦዘ-ም፡፫ ቁ፡፲፭ ያስረዳል<ref>በአንተና፡በሴቲቱ፡መካከል፥በዘርኽና፡በዘሯም፡መካከል፡ጠላትነትን፡አደርጋለኹ፤ርሱ፡ራስኽ ን፡ይቀጠቅጣል፥አንተም፡ሰኰናውን፡ትቀጠቅጣለኽ። </ref> '''[http://www.ethiopianorthodox.org/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን]''' ማርያምን በጣም ከመወደዷ የተነሳ ከ፻ በላይ በሰየመቻት ስሞቿ ትጠራታለች ('''[[የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች]]''')::
አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ።
ሙስሊሞች ደግሞ [[መሪማ የኢየሱስ (ኢሳ) እናት]] ይልዋታል።
በአለም ላይ ፫ ታላላቅ እምነቶች<ref>በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች<br>በካቶሊክ ክርስቲያኖች<br>በእስልምና</ref> ዘንድ እስዋም ልጅዋም ትልቅ ክብርና ቅድስና በተለይ ለልጇ መመለክ ገንዘባቸው ነው።
==Podcasts ለማዳመጥ==
<p>[https://castbox.fm/channel/ውዳሴ-ማርያም-፤-አንድምታ-id2592602?utm_source=website&utm_medium=dlink&utm_campaign=web_share&utm_content=%E1%8B%8D%E1%8B%B3%E1%88%B4%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D%20%E1%8D%A4%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%9D%E1%89%B3-CastBox_FM| ውዳሴ ማርያም እንድምታ podcast]
<p>[https://castbox.fm/channel/ቅዳሴ-ማርያም-አንድምታ-id2601455?utm_source=website&utm_medium=dlink&utm_campaign=web_share&utm_content=%E1%89%85%E1%8B%B3%E1%88%B4%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%9D%E1%89%B3-CastBox_FM| ቅዳሴ ማርያም እንድምታ podcast]
<p>[https://medhanealem.freetzi.com/SaintMariamogt.html '''ከድረገጾችዎ አንዱን ለማየት እዚህላይ ይጫኑ''']
== '''ክርስትና''' ==
በክርስትና እምነት ድንግል ማርያም ሰው ሁኖ የመጣዉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ከእግዚአብሔር '''[[አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ]]''' አንዱ '''ተወላዲ''' ማለትም ([[ወልድ]]) ሲሆን ፣ '''ወላዲ''' ደግሞ ([[አብ]]) ነው ፣ ቀጥሎም '''ሰራጺ''' (መንፈስ ቅዱስ) ይሆናል ፤ በተጨማሪ ወልድ ጌታ ወይም '''[[ክርስቶስ]]'''፡[[መሢሕ]] ይባላል። እናቱ ማርያም '''[[እግዚአብሔር]]''' የተባለውን ወልድ ለመውለድ ስለ ተመረጠች እና ብቁ ሆና ስለተገኘች ከሴቶች ሁሉ ይልቅ ብጹዕት ፣ ቅድስት ፣ በግሪክ [[ቴዎቶከስ]] ማለትም የእግዚአብሔር እናት ትባላለች።
=='''የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ'''==
'''[http://www.ethiopianorthodox.org/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን]''' ከ 34 ዓ.ም ጀምራ ክርስትናን በኢትዮጵያ ምድር የሰበከች ጥንታዊት ቤተክርስቲያን ሥትሆን ምድቧም ከ ኦርዮንታል አብያተ ክርስቲያናት ነው::
እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥላሴ አካላት አንዱ ወልድ፣ አምላክ ነው::ይህ አምላክም ወይም እግዚአብሔር ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ::በሌላ አገላለጽ አምላክ ሰው ሆነ::በዚህም ምክንያት ቅድስት ድንግል ማርያምን የጌታ እናት ወይም የእግዚአብሔር እናት(ወላዲተ አምላክ) ትባላለች::
ቤተክርስቲያኗ ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም አምላክ ፣ ወልደ አምላክ ፣ ወልደ ማርያም ፣ ወልድ፣ ቃል ብላ ትጠራዋለች::
ድንግል ማርያምን ደግሞ እመቤት ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ፣ እግዝእትነ ማርያም ፣ የጌታ እናት ፣ ወላዲተ አምላክ ፣ ቅድስት፣እመ ብርሃን ፣ እመ አምላክ፣ንጽሕተ ንጹሃን ቅድስተ ቅዱሳን፣ጽዮን ወዘተ በማለት ትጠራታለች::ቅድስት ድንግል ማርያምን አንዳንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች ከአዳም በደል ወይም ከ[[ጥንተ አብሶ ነጻ]] ሆና [[በአዳም ባህርይ እንደ እንቁ ስታበራ]] የኖረች አደፍ ጉድፍ የሌለባት ፣ ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ የነጻች ፣ እንደሆነች ያምናሉ። ሌላው ወገን ጥንተ አብሶ ነበራት ለዚህም ማስረጅያ "ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም" ተብሎ የሚጠራው በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ቁጥር 47 እግዚአብሔርን "መድኃኒቴ" ብላ ማመስገነዋ ነው። ሁለቱም ወገን ግን እግዚአብሔር ወልድ ሥጋዋን ከተዋሃደ በፊት እንዳነጻት ማደሪያው እንድትሆን እንዳስጌጣት ከወለድችሁም በኋላ በድንግልኗና በንፅህኗ እንደኖረች፣ ለዘለዓለም በዚሁ ሁኔታ ጸንታ እንደምትኖር ያምናሉ። ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች፣ የሰማይ የምድር ንግስት ፣ እንደሆነች ቤተክርስቲያን ታስተምራለችና ።
አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ [["ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል"]] ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ይህም መንፈስ ቅዱስ የሞላባት ወልድ የተዋሀዳት አብ የመረጣት ፍፁምነት የተገለፀባት ከሰው ሁሉ ተለይታ መከበር የሚገባት መሆኑዋን አረጋግጦ ያስረዳል ። <br />
<blockquote>
ጸሎተ ማርያም ሉቃስ ም፩ ፣ ፵፯ - ፶፭
ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ዠምሮ፡ትውልድ፡ዅሉ፦ብፅዕት፡ ይሉኛል፤ ብርቱ፡የኾነ፡ርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኀይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡
እስራኤልን፡ብላቴናውን፡ረድቷል።
</blockquote>
=='''የቅድስት ድንግል ማርያም ትውልድ'''==
ቅድስት ድንግል ማርያም አባቷ ኢያቄም እናቷ ደግሞ ሃና ይባላሉ::የተፀነሰቸው በእለተ እሁድ ነሐሴ ፯ ቀን ሲሆን የተወለደቸውም ግንቦት ፩ ነው::እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም የተወለደችበት እለት በአባት እናቷ ቤት ፍስሃ ደስታ ተደረገበት ፤ ቤቱንም ብርሃን መላው ፤ በ፰ኛውም ቀን [[ማርያም]] ብለው አወጡላት::ስለምን ማርያም ብለው አወጡላት ቢሉ:እነሆ በዚህ አለም ከሚመገቡት ሁሉ ምግብ ለአፍ የሚጥም ለልብ የሚመጥን [[ማር]] ነው:በገነትም በህይወት የተዘጋጁ ጻድቃን ቅዱሳን [[ያም]] የሚባል ምግብ አላቸው ::ከዚ ሁሉ የበለጥሽ የከበርሽ ነሽ ሲሉ ስለዚህ [[ማርያም]] ብለው አወጡላት::
እመቤታችን ማርያም ለእናት ለአባቷ አንዲት ስትሆን የተወለደቸው በጸሎት በመሆኑና የስለት ልጅ በመሆኗ እናትና አባቷ ለእግዚአብሔር በተሳሉት መሰረት ፫ ዓመት ሲሞላት ወደ ቤተመቅደስ ወሰደው ለካህኑ ለዘካርያስ አስረከቧት::እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደች በሦስት ዓመቷ እናቷ ሐና አባቷ ኢያቄምን፡- “ይህች ብላቴና ሆዷ ዘመድ ሳይወድ፣ አፏ እህል ሳይለምድ “ለእግዚአብሔር በገባነው ቃል መሠረት ወስደን ለቤተ መቅደስ አንሰጣትምን?” ‘የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሳ’ እንዲሉ አንዳች ነገር ብትሆንብን ከልጃችንም ከእግዚአብሔርም ሳንሆን እንዳንቀር” አለችው፡፡ እርሱም፡- “ፍቅርሽ ይለቅልሽ ብዬ ነው እንጂ እኔማ ፈቃዴ አይደለምን?” አላት፡፡ወላጆቿ ይህን ተነጋግረው እንዳበቁ ሕጻን ልጃቸውን ማርያምን ወስደው ለቤተ መቅደስ ሰጧት፡፡ በዚያን ጊዜ የነበረው ሊቀ ካህናት [[ዘካርያስ]] ይባላል፤ እርሱም ስለ ምግቧ ነገር ሊያስወስን መጥቅዕ (ደወል) ደውሎ ሕዝቡን ሰብስቦ እየተወያዩ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት [[ቅዱስ ፋኑኤል]] የሰማይ ኅብስትና የሰማይ ጽዋ ይዞ ከሰማይ ወርዶና ረብቦ ታየ፡፡ብላቴናይቱንም መልአኩ ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ደግሞ ጋርዶ በሰው ቁመት ያህል ከምድር አስለቅቆ ከፍ አድርጓትና መግቧት ዐረገ፡፡ ከዚህ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ “የምግቧ ነገር ከተያዘልንማ ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል” ብለው ሕጻን ማርያምን ከወላጆቿ ተቀብለው ወደ ቤተ መቅደስ አግብተዋት በዚያ ፲፪ ዓመት ኖራለች፡፡ይህም ሲደመር ጠቅላላ ፲፭ ዓመት ሆናት ማለት ነው::በዚህ ስዓት አይሁድ ከበተመቅደስ ትውጣልን ብለው አመለከቱ ፤ ለጻድቁ ለ[[ቅዱስ ዮሴፍ]]ም እንዲጠብቃት ታጨች ፤ መልአኩ [[ገብርኤል (መልዐክ)|ቅዱስ ገብርኤል]] አበሰራት::በ ፲፭ አመቷ [[ኢየሱስ|እግዚአብሔር ወልድ]]ን ፀነሰች::<br />
[[የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች]]:-
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን ማንነትን ይገልጻል ይላሉ፡፡በዚህም መሰረት ቤተክርስቲያኗ ለስመ ድንግል ማርያም ዘርፍ /ቅጽል/ አልያም ምትክ አድርጋ የምትጠቀምባቸው ምሥጢራዊና ረቂቅ ትርጉም ያላቸው ንጽሕናዋን፣ ቅድስናዋን፣ ድንግልናዋን፣ ብፅእናዋን ወዘተ የሚመሰክሩ በርካታ ስሞች ሰይማላታለች፡፡ከነዚህም መካከል ከብዙ በጥቂቱ:ምልዕተ ጸጋ ፣ እምነ /«ም» ጠብቆ ይነበብ/ ጽዮን ፣እመ ብርሃን ሰአሊተ ምሕረት ፣እመቤታችን ፣ቤዛዊተ ዓለም፣ ወላዲተ አምላክ ፣ኪዳነ ምሕረት ወዘተ..<br />
ቅድስት ድንግል ማርያም በ 64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ማረጓን ቤተክርስቲያኑ ታስተምራለች::
=='''ቅድስት ድንግል ማርያም በኢትዮጵያ'''==
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን [[ተአምረ ማርያም]] በሚባለው የጸሎት መጽሓፍ ቅድስት ድንግል ማርያም በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው በሕፃንነቱ ልጇን ጌታ ኢየሱስን እንዳይገድሉባት ከምድረ እስራኤል ስትሸሽ በግብጽ አልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ደርሳለች። ጌታ ኢየሱስ በእግሩ በመረገጡ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከአረጋዊው ከ[[ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ]] ከዘመዳቸው ከቅድስት ሰሎሜ ጋር በእንግድነት በመቀመጡ ምድረ ኢትዮጵያን ባርኳታል። እመቤታችንን በጭንቀቷ ሰዓት ይቺ ምድርና ሕዝቦቿ ስለተቀበሏት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአደራነት ወይም በአሥራትነት ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደሰጣት ቤተ ክርስቲያኒቷ ታስተምራለች።
በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ዘንድ እጅግ በጣም ልዩ ተወዳጅነትና ፍቅር ያላት በተለምዶ እንኳን እምዬ እናታችን እመቤታችን ወይም በመዓረግ ስሞቿ ኪዳነ ምሕረት ወላዲተ አምላክ እመብርሃን ተብላ ትጠራለች። ከኃይማኖትም ባሻገር በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ባህልም ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ቦታ አላት። ለምሳሌ አንዲት እርጉዝ ሴት ልትወልድ ስትል «ድንግል ማርያም ትቅረብሽ» ስትወልድም «እንኳን ማርያም ማረችሽ» በአራስ ቤትም ሳለች «ድንግል ማርያም በሽልም ታውጣሽ» ትባላለች። አንድ ሰው ገላው ላይ ሲወለድ የነበረ ጥቁር ምልክት ቢኖረው «ድንግል ማርያም እዚህ ስምሃለች» ይባላል።
==ፍልሰታ==
<p><center>ጾመ ፍልሰታ</center>
[[ስዕል:የቅድስት ድንግል ማርያም እገት.jpeg|thumb|የእመቤታችን እርገቷ]]
ፍልሰታ የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ስር ከነበረበት መነሳቱን ለማመልከት ይነገራል።
ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ 8 ቀን አስከ
ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው።
ኃይማኖታዊ መሠረት
እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች# <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት : ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር : hዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷ä ዓመት ዕድሜዋ በ፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፰ö ነው የመልክአ ማርያም ቁጥርም ፷ö ነው።
ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ፡ ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል :: የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል ። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ Aስከ ነሐሴ ፲ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብ» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች» በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው።
በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ።
የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች።
ንጉስ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፩ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውብቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ ወዳጄ ...ዉበቴ»" የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት # ክቡር ዳዊት መዝሙር ö ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም።
== '''እስልምና''' ==
የማርያምን ድንግል ሁና እየሱስን ወይንም እነሱ እንደሚሉት ኢሳ (አ.ሰ)ን እንደወለደች ብሎም በነሱ እምነት አራት ተብለዉ ከተጠቀሱ ምርጥ ሴቶች ዉስጥ አንድዋ ነች። ነገር ግን ኢሳን የ[[አላህ]] መልዕክተኛ ነዉ ሲሉት፣ አላህም ፈጣሪዉ እንጅ ልጁ አይደለም ባዮች ናቸው። በ[[ቁርአን]] ምክንያት አምላክ አይወልድም አይወለድም፤ ይህም ለአላህ የማይገባው ሥራ ነው ይላሉ።
== '''ሥዕሎች''' ==
[[ስዕል:ድንግል ማርያም.jpeg|none|thumb|«ምስለ ፍቁር ወልዳ» የሚባለው ሥዕል ልጇን ጌታ ኢየሱስን አቅፋ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ [[ሚካኤል]]ና ቅዱስ [[ገብርኤል (መልዐክ)]] ግራና ቀኝ ቆመው]]
[[ስዕል:ቁስቋም ማርያም.jpeg|none|thumb|ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታ ኢየሱስን ይዛ ወደ ኢትዮጵያና ኤርትራ ተሰዳ እንደመጣች የሚገልጽ ሥዕል]]
[[ስዕል:አክሱም ፅዮን ማርያም.jpeg|none|thumb|በኢትዮጵያ ውስጥ አለች የምትባለው ገዳም ለቅድስት ድንግል ማርያም ስምና ክብር የተሠራች የ[[አክሱም]] ፅዮን ቤተክርስቲያን። ]]
==ማጣቀሻ==
[[መደብ:እስልምና]]
{{መደብ:ክርስትና}}
n2urjluqb6gymiubnp05229zdxhrdoa
ቅዱስ መርቆሬዎስ
0
49612
372117
371945
2022-07-22T19:40:40Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox
|abovestyle=background:#FFD300
|above=ቅዱስ መርቆሬዎስ
|image=[[ስዕል:ቅዱስ ማርቆርዮስ.jpeg|200px]]
|caption=የሮም ንጉሥ የዳክዮስ ጦር ጠቅላይ አዛዥ
|headerstyle=background:#BCD4E6
|header1=ሰማዕት
|headerstyle=background:#FFD300
|header16=<span style="color:#0048BA">
</span>
|label2=የተወለደበት ዘመን
|data2= ፪፻፸፩ ዓም <ref> ታሪካቸው በኢትዮጵያ [http://www.stmichaeleoc.org/Synaxarium/Archive.htm ሥንክሳር] ወይም [https://play.google.com/store/apps/details?id=patristicpublishing.eth Ethiopian Synaxarium] በኅዳር ፳፭ የሰማዕታትና ቅዱሳን ታሪክ ውስጥ ይነበባል</ref>
|label3=የትውልድ ቦታ
|data3=[[ሮም]]
|label4=የመጀመሪያ ስሙ
|data4=ፒሉፖዴር
|label5=የክርስትና ስሙ
|data5=መርቆሬዎስ
|label6=የአባት ስም
|data6=ሎሪዮ
|label7=የእናት ስም
|data7=ክሪስቲና
|label8=ሃይማኖት
|data8=[[ክርስትና]]
|label9=በዓለ ንግሥ
|data9=ባረፈበት ቀን [[ኅዳር ፳፭ ቀን]] ፫፻፲ ዓም
|label10=የሚከበረው
|data10=በ[[ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን]]<br>በምሥራቅም በምዕራብም ቤተክርስቲያኖች <br> [[ቤተ መርቆሬዎስ|ቤተ መርቆሬዎስን ይመልከቱ]]
|header11=}}
የመጀመሪያ ስሙ [[ፒሉፖዴር]] ይባል ነበር በላቲን ሲሆን ትርጔሜውም ታማኝ ሐቀኛ ማለት ነው ። የክርስትና ስሙ [[መርቆሬዎስ]] ሙያውም [[ውትድርና]] ዜግነቱም [[ሮም|ሮማዊ]] ነው ።
ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል።
እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ።
<h5>ለምን መከራን ተቀበለ?</h5>
1 ስለመንግስተ ሰማያት ሐዋ14÷22
2 ሃይማኖትን ለመመስከር ማቴ10÷32
3 አርአያ ለመሆን
4 እውነትን በሐሰት መለወጥ ስላልፈለገ 2ተኛ ቆሮ 5÷13
==ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ==
መርቆሬዎስም ማለት የእየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ሲሆን ይህም ቋሚ መጠርያ ስሙ ሆኖ ቀረ ። በእንግሊዞች የተጻፈው ገድለ ቅዱሳን [[ባዮግራፊ ኦፍ ሴንትስ]] እንደሚለው ዜግነቱ ኢጣሊያዊ ሲሆን ስሙንም መርኮርዮ ብሎታል የእባቱንም ስም ሎሪዮ የእናቱንም ስም ክርስቲና እንደሆነ ገልጿል ። በያመቱ ኅዳር ፳፭ ቀን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ የአባቱን ስም ኖኅ የናቱን ስም ታቦት የራሱንም ስም መርቆሬዮስ እንደሆነ ይገልጻል ። በዚያም ዘመን ውትድርና የተወደደና የተከበረ ሙያ
[https://play.google.com/store/apps/details?id=patristicpublishing.eth ስለነበር] መርቆሬዎስም ዳክዮስ ለተባለ ንጉሥ ወታደር ሆነ ዕለት ከዕለት የሚያሳየው ወታደራዊ ሥነ ሥርዓትና በሚፈጽመው ጀብዱ ከሌሎች ወታደሮች ይልቅ ተወዳጅነትና ባለሟልነት አገኘ ፤ ዳክዮስ ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ቁጥር ድል ያስገኘለትን '''[[እግዚአብሔር]]'''ን ዘንግቶ ድል የሚያስገኝለት ጣዖት እየመሰለው ከጦርነት ሲመለስ ለጣዖት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ ነበረው ከዕለታት አንድ ቀን ዳክዮስ መርቆርዮስን አስከትሎ ዘመተና ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ጊዜ እንደ ልማዱ ለማይሰማውና ለማይናገረው ጣዖት ከስግደትና ከጸሎት ጋር የምስጋና መሥዋት አቀረበ ከደስታው ብዛት የተነሣ ብዙ እንሰሳት በየዓይነቱ እየመረጠ ሠዋ።<br>
[[ስዕል:መርቆርዮስ በጣርነት.png|160px|height:84px|thumb|የመርቆሬዎስ ጀግንነትን የሚገልጽ ስዕል]]
==ሰማዕት የሆነበት ምክኒያት==
ቅዱስ መርቆሬዎስም ይህን በማየቱ ሰው ድል ለሰጠው ለእግዚአብሔር በመስገድና እሱንም በማመስገን ፈንታ እንዴት ሰው ለሠራው ጣዖት ይሰግዳል ? በማለት ቅር ስላለውና አረማዊነቱንም በግልጽ ስላወቀ በዚህ ተቀይሞ ወደተዘጋጀው የድል ግብዣ ሳይሄድ ቀረ በዚሁ ጊዜ አብረው የዘመቱ ሌሎች የሠራዊቱ አባሎች እኛ ለምታመልከው ጣዖት ስንሰግድና ባደረከው ታላቅ ግብዣ ትእዛዝህን አክብረን ስንገኝ ታማኝ ባለሟልህ መርቆርዎስ ትእዛዝህን በመናቅና አንተን ባለማክበር እነሆ አልተገኘም እንዲያውም ለጣዖትህ መስገድ የማይፈልግ ሳይሆን አይቀርም አስተያየት ስጥበት ብለው በንጉሡ መሾምና መወደድ የሚፈልጉ ሰዎች አሳጡት።
{|
[[ስዕል:ቅዱስ ማርቆርዮስ፩.jpeg|thumb|150px|ቅዱስ መርቆሬዎስ በጣር ግምባር ውጊያ ላይ]]
ዳክዮስም በመርቆሬዎስ ላይ የቀረበውን ክስ ካዳመጠ በኋላ መርቆርዎስን አስጠርቶ ስለምን ለጣዖት እንዳልሰገደና መሥዋዕት እንዳላቀረበ እንዲሁም ወደ ግብር እንዳልመጣ ጠየቀው ። እሱም ሳይፈራ በድፍረት እንኳንስ እኔ ለጣዖትህ ልሰግድና መሥዋዕት ላቀርብ አንተም እንዲህ በማድረግህ አዝናለሁ ብሎ መለሰለት ፤ ነገር ግን እኔ '''[[እግዚአብሔር]]ን''' አመልካለሁ ፤ ለሱም እሰግዳለሁ ይኸው መሣሪያህንና ትጥቅህን ተረከበኝ ብሎ አውልቆ ወረወረለት።ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ መስቀል መሸከሙንና ወንጌል ይዞ የክርስቶስ ወታደርነቱን በመግለጹ ዳክዮስ በጣም ተናደደ በግርፋትና በእስራት እንዲያሰቃዩትም አዘዘ ። በእስር ቤት ሲሰቃይ ሳለ የሮም ዜጋ ሆኖ በመታሰሩና በመሰቃየቱ የሮም ዜጋ መታሰሩንና መሰቃየቱን ያወቁ መገረፉንም የሰሙ እንደሆነ ሮማውያን ታላቅ ኃይል ያስከትሉብናል የሚነሣውንም ዐመፅ ለመቋቋም ስለማይቻል ግዛታችን ሰፊ ነውና በጽኑ እስራትና በግዞት እንዲሰቃይ ወደ ቂሣርያ እንላከው ሲሉ ተማከሩ ። ዳክዮስና አማካሪዎቹ በዚሁ በመስማማታቸው ታማኙ ሰማዕት ወደዚችው አገር ተላከ ቂሣርያም የምትገኘው [[እስራኤል|በምድረእስራኤል]] ነው ።
==ማርቆሬዎስ በቄሣሪያ==
በቂሣርያም እስር ቤት ስቃዩንና መከራውን ተቋቋመ ወንጌል እየሰበከና እስረኞችን ከአረማዊነት ወደ ክርስትና እምነት እየለወጠ ስላስቸገራቸው ኅዳር ፳፭ ቀን ፫፻፲ ዓ/ም በሰይፍ ተከልሎ በሰማዕትነት ዐረፈ።
እንደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስለ ታማኝ ምስክር ዮሐንስ በራእዩ በም:፫፥፲፪ እንዲህ ሲል ጽፎታል፡
<blockquote>
'''"ድል የነሣውን በአምላኬ መቅደስ ዐምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ ፤ ወደፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም የአምላኬን ከተማ ስም ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌም አዲሲቱን ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ..."ብሏል።'''
</blockquote>እርግጥም ቅዱስ መርቆሬዎስ ወደ አዲሲቱ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም ገብቷል።
== መረጃ ==
[[መደብ:ክርስትና]]
[[መደብ:ተዋህዶ]]
7iqi7j5w4kx6jkwv5lzvkx2uvx0i3tu
372118
372117
2022-07-22T19:42:33Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox
|abovestyle=background:#FFD300
|above=ቅዱስ መርቆሬዎስ
|image=[[ስዕል:ቅዱስ ማርቆርዮስ.jpeg|200px]]
|caption=የሮም ንጉሥ የዳክዮስ ጦር ጠቅላይ አዛዥ
|headerstyle=background:#BCD4E6
|header1=ሰማዕት
|headerstyle=background:#FFD300
|header16=<span style="color:#0048BA">
</span>
|label2=የተወለደበት ዘመን
|data2= ፪፻፸፩ ዓም <ref> ታሪካቸው በኢትዮጵያ [http://www.stmichaeleoc.org/Synaxarium/Archive.htm ሥንክሳር] ወይም [https://play.google.com/store/apps/details?id=patristicpublishing.eth Ethiopian Synaxarium] በኅዳር ፳፭ የሰማዕታትና ቅዱሳን ታሪክ ውስጥ ይነበባል</ref>
|label3=የትውልድ ቦታ
|data3=[[ሮም]]
|label4=የመጀመሪያ ስሙ
|data4=ፒሉፖዴር
|label5=የክርስትና ስሙ
|data5=መርቆሬዎስ
|label6=የአባት ስም
|data6=ሎሪዮ
|label7=የእናት ስም
|data7=ክሪስቲና
|label8=ሃይማኖት
|data8=[[ክርስትና]]
|label9=በዓለ ንግሥ
|data9=ባረፈበት ቀን [[ኅዳር ፳፭ ቀን]] ፫፻፲ ዓም
|label10=የሚከበረው
|data10=[http://www.ethiopianorthodox.org/ በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን]<br>በ[[ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን]]<br>በምሥራቅም በምዕራብም ቤተክርስቲያኖች <br> [[ቤተ መርቆሬዎስ|ቤተ መርቆሬዎስን ይመልከቱ]]
|header11=}}
የመጀመሪያ ስሙ [[ፒሉፖዴር]] ይባል ነበር በላቲን ሲሆን ትርጔሜውም ታማኝ ሐቀኛ ማለት ነው ። የክርስትና ስሙ [[መርቆሬዎስ]] ሙያውም [[ውትድርና]] ዜግነቱም [[ሮም|ሮማዊ]] ነው ።
ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል።
እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ።
<h5>ለምን መከራን ተቀበለ?</h5>
1 ስለመንግስተ ሰማያት ሐዋ14÷22
2 ሃይማኖትን ለመመስከር ማቴ10÷32
3 አርአያ ለመሆን
4 እውነትን በሐሰት መለወጥ ስላልፈለገ 2ተኛ ቆሮ 5÷13
==ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ==
መርቆሬዎስም ማለት የእየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ሲሆን ይህም ቋሚ መጠርያ ስሙ ሆኖ ቀረ ። በእንግሊዞች የተጻፈው ገድለ ቅዱሳን [[ባዮግራፊ ኦፍ ሴንትስ]] እንደሚለው ዜግነቱ ኢጣሊያዊ ሲሆን ስሙንም መርኮርዮ ብሎታል የእባቱንም ስም ሎሪዮ የእናቱንም ስም ክርስቲና እንደሆነ ገልጿል ። በያመቱ ኅዳር ፳፭ ቀን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ የአባቱን ስም ኖኅ የናቱን ስም ታቦት የራሱንም ስም መርቆሬዮስ እንደሆነ ይገልጻል ። በዚያም ዘመን ውትድርና የተወደደና የተከበረ ሙያ
[https://play.google.com/store/apps/details?id=patristicpublishing.eth ስለነበር] መርቆሬዎስም ዳክዮስ ለተባለ ንጉሥ ወታደር ሆነ ዕለት ከዕለት የሚያሳየው ወታደራዊ ሥነ ሥርዓትና በሚፈጽመው ጀብዱ ከሌሎች ወታደሮች ይልቅ ተወዳጅነትና ባለሟልነት አገኘ ፤ ዳክዮስ ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ቁጥር ድል ያስገኘለትን '''[[እግዚአብሔር]]'''ን ዘንግቶ ድል የሚያስገኝለት ጣዖት እየመሰለው ከጦርነት ሲመለስ ለጣዖት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ ነበረው ከዕለታት አንድ ቀን ዳክዮስ መርቆርዮስን አስከትሎ ዘመተና ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ጊዜ እንደ ልማዱ ለማይሰማውና ለማይናገረው ጣዖት ከስግደትና ከጸሎት ጋር የምስጋና መሥዋት አቀረበ ከደስታው ብዛት የተነሣ ብዙ እንሰሳት በየዓይነቱ እየመረጠ ሠዋ።<br>
[[ስዕል:መርቆርዮስ በጣርነት.png|160px|height:84px|thumb|የመርቆሬዎስ ጀግንነትን የሚገልጽ ስዕል]]
==ሰማዕት የሆነበት ምክኒያት==
ቅዱስ መርቆሬዎስም ይህን በማየቱ ሰው ድል ለሰጠው ለእግዚአብሔር በመስገድና እሱንም በማመስገን ፈንታ እንዴት ሰው ለሠራው ጣዖት ይሰግዳል ? በማለት ቅር ስላለውና አረማዊነቱንም በግልጽ ስላወቀ በዚህ ተቀይሞ ወደተዘጋጀው የድል ግብዣ ሳይሄድ ቀረ በዚሁ ጊዜ አብረው የዘመቱ ሌሎች የሠራዊቱ አባሎች እኛ ለምታመልከው ጣዖት ስንሰግድና ባደረከው ታላቅ ግብዣ ትእዛዝህን አክብረን ስንገኝ ታማኝ ባለሟልህ መርቆርዎስ ትእዛዝህን በመናቅና አንተን ባለማክበር እነሆ አልተገኘም እንዲያውም ለጣዖትህ መስገድ የማይፈልግ ሳይሆን አይቀርም አስተያየት ስጥበት ብለው በንጉሡ መሾምና መወደድ የሚፈልጉ ሰዎች አሳጡት።
{|
[[ስዕል:ቅዱስ ማርቆርዮስ፩.jpeg|thumb|150px|ቅዱስ መርቆሬዎስ በጣር ግምባር ውጊያ ላይ]]
ዳክዮስም በመርቆሬዎስ ላይ የቀረበውን ክስ ካዳመጠ በኋላ መርቆርዎስን አስጠርቶ ስለምን ለጣዖት እንዳልሰገደና መሥዋዕት እንዳላቀረበ እንዲሁም ወደ ግብር እንዳልመጣ ጠየቀው ። እሱም ሳይፈራ በድፍረት እንኳንስ እኔ ለጣዖትህ ልሰግድና መሥዋዕት ላቀርብ አንተም እንዲህ በማድረግህ አዝናለሁ ብሎ መለሰለት ፤ ነገር ግን እኔ '''[[እግዚአብሔር]]ን''' አመልካለሁ ፤ ለሱም እሰግዳለሁ ይኸው መሣሪያህንና ትጥቅህን ተረከበኝ ብሎ አውልቆ ወረወረለት።ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ መስቀል መሸከሙንና ወንጌል ይዞ የክርስቶስ ወታደርነቱን በመግለጹ ዳክዮስ በጣም ተናደደ በግርፋትና በእስራት እንዲያሰቃዩትም አዘዘ ። በእስር ቤት ሲሰቃይ ሳለ የሮም ዜጋ ሆኖ በመታሰሩና በመሰቃየቱ የሮም ዜጋ መታሰሩንና መሰቃየቱን ያወቁ መገረፉንም የሰሙ እንደሆነ ሮማውያን ታላቅ ኃይል ያስከትሉብናል የሚነሣውንም ዐመፅ ለመቋቋም ስለማይቻል ግዛታችን ሰፊ ነውና በጽኑ እስራትና በግዞት እንዲሰቃይ ወደ ቂሣርያ እንላከው ሲሉ ተማከሩ ። ዳክዮስና አማካሪዎቹ በዚሁ በመስማማታቸው ታማኙ ሰማዕት ወደዚችው አገር ተላከ ቂሣርያም የምትገኘው [[እስራኤል|በምድረእስራኤል]] ነው ።
==ማርቆሬዎስ በቄሣሪያ==
በቂሣርያም እስር ቤት ስቃዩንና መከራውን ተቋቋመ ወንጌል እየሰበከና እስረኞችን ከአረማዊነት ወደ ክርስትና እምነት እየለወጠ ስላስቸገራቸው ኅዳር ፳፭ ቀን ፫፻፲ ዓ/ም በሰይፍ ተከልሎ በሰማዕትነት ዐረፈ።
እንደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስለ ታማኝ ምስክር ዮሐንስ በራእዩ በም:፫፥፲፪ እንዲህ ሲል ጽፎታል፡
<blockquote>
'''"ድል የነሣውን በአምላኬ መቅደስ ዐምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ ፤ ወደፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም የአምላኬን ከተማ ስም ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌም አዲሲቱን ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ..."ብሏል።'''
</blockquote>እርግጥም ቅዱስ መርቆሬዎስ ወደ አዲሲቱ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም ገብቷል።
== መረጃ ==
[[መደብ:ክርስትና]]
[[መደብ:ተዋህዶ]]
hy3wd4c1rfbu8zinshn4e5puismap9u
ቅዱስ ቂርቆስ ወእሙ ቅድስት እያሉጣ
0
50453
372112
362531
2022-07-22T18:15:34Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#7CB9E8|above=ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ|image=[[ስዕል:ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ.jpeg|264px|center|ቂርቆስ ኢያሉጣ ቅዱሳን ሰማዕታት ]]|caption=|headerstyle=background:#7CB9E8|header1= ድንቅ የእናትና ልጅ እምነት|headerstyle=background:#7CB9E8|header10=<span style="color:#FFBF00">
</span>|label1=|data1=|label2=የኖሩበት ዘመን|data2=፬ኛው ክፍለ ዘመን |label3=የትውልድ ሀገር|data3=[[ሮም]]|label4=የአባት ስም|data4=ቆዝሞስ|label5=የእናትስም|data5=ቅድስት እያሉጣ|label6=በዓለ ንግሥ|data6=[[ሐምሌ ፲፭]] ቀን|label7=የሚከበሩት|data7=በኢትዮጵያ ርትዕት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን <br> በቤዛንቲያን ቤተክርስቲያን <br> በካቶሊክ ቤተክርስቲያን <br> በኮፕት ቤተክርስቲያን <br> በምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን|label8=የሚታወቁት|data8=በእግዚአብሔር ኃይል [[ገብርኤል (መልዐክ)|በቅዱስ ገብርኤል]] አማካኝነት እንደ እሳት ከፈላ ውሀ ውስጥ ያለምንም ጉዳት መውጣት ። |captionstyle=
|header9=}}
'''ቅዱስ ቂርቆስ''' (በእንግሊዘኛ :[[:en:Cyricus and Julitta|Cyricus]]) (በአራማይክ : ܡܪܝ ܩܘܪܝܩܘܣ ܣܗܕܐ Mar Quriaqos Sahada ፤ በተጨማሪ Quiricus Cyriacus Quiriac) ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው ። አባቱ ቆዝሞስ ይባላል ። እናቱ ቅድስት እያሉጣ (በእንግሊዘኛ : [[:en:Cyricus and Julitta|Julitta]]) (በግሪክ: ουλίττα) (በአራማይክ ܝܘܠܝܛܐ, : Yolitha) በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች ። እኒህ ሁለት ሰማዕታት [[ማርያም|የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናቸው።]]
የሚታወቁበትም ታሪካቸው እንደሚከተለው ነው ።
ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ፳ኛው ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክኒያት "የጣዖታት ቤቶች ሁሉ ይከፈቱ ፣ ቤተክርስቲያኖች ሁሉ ይዘጉ" ብሎ በ፫፻፫ ዓ ም አወጀ ። በዚህ ጊዜ እኩሌቶቹ ተሰደዱ ቅድስት እያሉጣም ልጇ የ፫ ዓመት ሕፃን ነበረና ለርሱ ብላ ከሁለት አገልጋዮችዋ ጋር ሆና ወደ ኢቆንዮን ሸሸች ።
የዚችም ሀገር ክርስቲያኖች የባሰ ስቃይ ውስጥ ነበሩ ። መስፍነ ብሔሩ እስክንድሮስም ፣ ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ አላት ። እሷም ዓይን እያለው የማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች ። አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት ። እስኪ ይህንን ሕፃን ጠይቀው አለችው ። አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው ። መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ፣ ራሳቸውን እንኳን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም አለው ። እንዲህም በመለሰለት ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውሀ አፍልታቹህ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው አለ ታዛዦቹም በብረት ጋን ውሀ አፈሉ ድምፁም እንደ ክረምት ነጎድጉዋድ ፵፪ ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር ።
ሊከቷቸውም ሲወስዱዋቸው እያሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ቂርቆስ ግን ፍርሀቷን አርቅላት እያለ ይጸልይላት እሷንም <blockquote>"ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ በዚያውስ ላይ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላካችን እኛንስ ያድነን የለምን" </blockquote> እያለ እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ከዚህም በኋላ እሷም ጨክና በፍፁም ልብ ሆነው ተያይዘው ከፈላው ውኃ ውስጥ ገብተዋል ።"
በዚህም ጊዜም ከዐላውያን ነገሥታት ከዐላውያን መናፍስት ቀርበው የመሰከሩለት በስሙ መከራ የተቀበሉለት [[ኢየሱስ|ጌታ መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ]] [[ገብርኤል (መልዐክ)|ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልን]] ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል ።
በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይለበለብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው አንገታቸውን ለስለት ሰጥተው በሰማዕትነት ዐርፈዋል ።
[[ስዕል:የቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እያሉጣ ሰማዕትነት.jpeg|250px|thumb|እውነት ተናግረው ፃድቃን ሰማዕትነታቸውን እንደተጎናጸፉ]]
ከመዝገበ ታሪክ
{{መደብ:ክርስትና}}
1wu1kuifnoqrvol8cevw1drfffhqloy
372113
372112
2022-07-22T19:26:22Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#7CB9E8|above=ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ|image=[[ስዕል:ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ.jpeg|264px|center|ቅዱሳን ሰማዕታት ]]|caption=|headerstyle=background:#7CB9E8|header1= ድንቅ የእናትና ልጅ እምነት|headerstyle=background:#7CB9E8|header10=<span style="color:#FFBF00">
</span>|label1=|data1=|label2=የኖሩበት ዘመን|data2=፬ኛው ክፍለ ዘመን |label3=የትውልድ ሀገር|data3=[[ሮም]]|label4=የአባት ስም|data4=ቆዝሞስ|label5=የእናትስም|data5=ቅድስት እያሉጣ|label6=በዓለ ንግሥ|data6=[[ሐምሌ ፲፭]] ቀን|label7=የሚከበሩት|data7=በኢትዮጵያ ርትዕት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን <br> በቤዛንቲያን ቤተክርስቲያን <br> በካቶሊክ ቤተክርስቲያን <br> በኮፕት ቤተክርስቲያን <br> በምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን|label8=የሚታወቁት|data8=በእግዚአብሔር ኃይል [[ገብርኤል (መልዐክ)|በቅዱስ ገብርኤል]] አማካኝነት እንደ እሳት ከፈላ ውሀ ውስጥ ያለምንም ጉዳት መውጣት ። |captionstyle=
|header9=}}
'''ቅዱስ ቂርቆስ''' (በእንግሊዘኛ :[[:en:Cyricus and Julitta|Cyricus]]) (በአራማይክ : ܡܪܝ ܩܘܪܝܩܘܣ ܣܗܕܐ Mar Quriaqos Sahada ፤ በተጨማሪ Quiricus Cyriacus Quiriac) ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው ። አባቱ ቆዝሞስ ይባላል ። እናቱ ቅድስት እያሉጣ (በእንግሊዘኛ : [[:en:Cyricus and Julitta|Julitta]]) (በግሪክ: ουλίττα) (በአራማይክ ܝܘܠܝܛܐ, : Yolitha) በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች ። እኒህ ሁለት ሰማዕታት [[ማርያም|የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናቸው።]]
የሚታወቁበትም ታሪካቸው እንደሚከተለው ነው ።
ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ፳ኛው ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክኒያት "የጣዖታት ቤቶች ሁሉ ይከፈቱ ፣ ቤተክርስቲያኖች ሁሉ ይዘጉ" ብሎ በ፫፻፫ ዓ ም አወጀ ። በዚህ ጊዜ እኩሌቶቹ ተሰደዱ ቅድስት እያሉጣም ልጇ የ፫ ዓመት ሕፃን ነበረና ለርሱ ብላ ከሁለት አገልጋዮችዋ ጋር ሆና ወደ ኢቆንዮን ሸሸች ።
የዚችም ሀገር ክርስቲያኖች የባሰ ስቃይ ውስጥ ነበሩ ። መስፍነ ብሔሩ እስክንድሮስም ፣ ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ አላት ። እሷም ዓይን እያለው የማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች ። አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት ። እስኪ ይህንን ሕፃን ጠይቀው አለችው ። አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው ። መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ፣ ራሳቸውን እንኳን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም አለው ። እንዲህም በመለሰለት ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውሀ አፍልታቹህ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው አለ ታዛዦቹም በብረት ጋን ውሀ አፈሉ ድምፁም እንደ ክረምት ነጎድጉዋድ ፵፪ ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር ።
ሊከቷቸውም ሲወስዱዋቸው እያሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ቂርቆስ ግን ፍርሀቷን አርቅላት እያለ ይጸልይላት እሷንም <blockquote>"ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ በዚያውስ ላይ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላካችን እኛንስ ያድነን የለምን" </blockquote> እያለ እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ከዚህም በኋላ እሷም ጨክና በፍፁም ልብ ሆነው ተያይዘው ከፈላው ውኃ ውስጥ ገብተዋል ።"
በዚህም ጊዜም ከዐላውያን ነገሥታት ከዐላውያን መናፍስት ቀርበው የመሰከሩለት በስሙ መከራ የተቀበሉለት [[ኢየሱስ|ጌታ መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ]] [[ገብርኤል (መልዐክ)|ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልን]] ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል ።
በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይለበለብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው አንገታቸውን ለስለት ሰጥተው በሰማዕትነት ዐርፈዋል ።
[[ስዕል:የቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እያሉጣ ሰማዕትነት.jpeg|250px|thumb|እውነት ተናግረው ፃድቃን ሰማዕትነታቸውን እንደተጎናጸፉ]]
ከመዝገበ ታሪክ
{{መደብ:ክርስትና}}
jpyd9hja8ck40cwd7dyns4p3xycmeyn
372115
372113
2022-07-22T19:34:55Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#7CB9E8|above=ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ|image=[[ስዕል:ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ.jpeg|264px|center|ቅዱሳን ሰማዕታት ]]|caption=|headerstyle=background:#7CB9E8|header1= ድንቅ የእናትና ልጅ እምነት|headerstyle=background:#7CB9E8|header10=<span style="color:#FFBF00">
</span>|label1=|data1=|label2=የኖሩበት ዘመን|data2=፬ኛው ክፍለ ዘመን |label3=የትውልድ ሀገር|data3=[[ሮም]]|label4=የአባት ስም|data4=ቆዝሞስ|label5=የእናትስም|data5=ቅድስት እያሉጣ|label6=በዓለ ንግሥ|data6=[[ሐምሌ ፲፭]] ቀን|label7=የሚከበሩት|data7=[http://www.ethiopianorthodox.org/ በኢትዮጵያ ርትዕት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን] <br> በቤዛንቲያን ቤተክርስቲያን <br> በካቶሊክ ቤተክርስቲያን <br> በኮፕት ቤተክርስቲያን <br> በምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን|label8=የሚታወቁት|data8=በእግዚአብሔር ኃይል [[ገብርኤል (መልዐክ)|በቅዱስ ገብርኤል]] አማካኝነት እንደ እሳት ከፈላ ውሀ ውስጥ ያለምንም ጉዳት መውጣት ። |captionstyle=
|header9=}}
'''ቅዱስ ቂርቆስ''' (በእንግሊዘኛ :[[:en:Cyricus and Julitta|Cyricus]]) (በአራማይክ : ܡܪܝ ܩܘܪܝܩܘܣ ܣܗܕܐ Mar Quriaqos Sahada ፤ በተጨማሪ Quiricus Cyriacus Quiriac) ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው ። አባቱ ቆዝሞስ ይባላል ። እናቱ ቅድስት እያሉጣ (በእንግሊዘኛ : [[:en:Cyricus and Julitta|Julitta]]) (በግሪክ: ουλίττα) (በአራማይክ ܝܘܠܝܛܐ, : Yolitha) በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች ። እኒህ ሁለት ሰማዕታት [[ማርያም|የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናቸው።]]
የሚታወቁበትም ታሪካቸው እንደሚከተለው ነው ።
ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ፳ኛው ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክኒያት "የጣዖታት ቤቶች ሁሉ ይከፈቱ ፣ ቤተክርስቲያኖች ሁሉ ይዘጉ" ብሎ በ፫፻፫ ዓ ም አወጀ ። በዚህ ጊዜ እኩሌቶቹ ተሰደዱ ቅድስት እያሉጣም ልጇ የ፫ ዓመት ሕፃን ነበረና ለርሱ ብላ ከሁለት አገልጋዮችዋ ጋር ሆና ወደ ኢቆንዮን ሸሸች ።
የዚችም ሀገር ክርስቲያኖች የባሰ ስቃይ ውስጥ ነበሩ ። መስፍነ ብሔሩ እስክንድሮስም ፣ ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ አላት ። እሷም ዓይን እያለው የማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች ። አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት ። እስኪ ይህንን ሕፃን ጠይቀው አለችው ። አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው ። መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ፣ ራሳቸውን እንኳን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም አለው ። እንዲህም በመለሰለት ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውሀ አፍልታቹህ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው አለ ታዛዦቹም በብረት ጋን ውሀ አፈሉ ድምፁም እንደ ክረምት ነጎድጉዋድ ፵፪ ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር ።
ሊከቷቸውም ሲወስዱዋቸው እያሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ቂርቆስ ግን ፍርሀቷን አርቅላት እያለ ይጸልይላት እሷንም <blockquote>"ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ በዚያውስ ላይ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላካችን እኛንስ ያድነን የለምን" </blockquote> እያለ እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ከዚህም በኋላ እሷም ጨክና በፍፁም ልብ ሆነው ተያይዘው ከፈላው ውኃ ውስጥ ገብተዋል ።"
በዚህም ጊዜም ከዐላውያን ነገሥታት ከዐላውያን መናፍስት ቀርበው የመሰከሩለት በስሙ መከራ የተቀበሉለት [[ኢየሱስ|ጌታ መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ]] [[ገብርኤል (መልዐክ)|ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልን]] ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል ።
በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይለበለብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው አንገታቸውን ለስለት ሰጥተው በሰማዕትነት ዐርፈዋል ።
[[ስዕል:የቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እያሉጣ ሰማዕትነት.jpeg|250px|thumb|እውነት ተናግረው ፃድቃን ሰማዕትነታቸውን እንደተጎናጸፉ]]
ከመዝገበ ታሪክ
{{መደብ:ክርስትና}}
87hw52ywyxqtb0oun5xf9qghiwx9tcm
372116
372115
2022-07-22T19:38:08Z
ክርስቶስሰምራ
27288
wikitext
text/x-wiki
{{infobox|abovestyle=background:#7CB9E8|above=ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ|image=[[ስዕል:ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እያሉጣ.jpeg|264px|center|ቅዱሳን ሰማዕታት ]]|caption=|headerstyle=background:#7CB9E8|header1= ድንቅ የእናትና ልጅ እምነት|headerstyle=background:#7CB9E8|header10=<span style="color:#FFBF00">
</span>|label1=|data1=|label2=የኖሩበት ዘመን|data2=፬ኛው ክፍለ ዘመን |label3=የትውልድ ሀገር|data3=[[ሮም]]|label4=የአባት ስም|data4=ቆዝሞስ|label5=የእናትስም|data5=ቅድስት እያሉጣ|label6=በዓለ ንግሥ|data6=[[ሐምሌ ፲፭]] ቀን|label7=የሚከበሩት|data7=[http://www.ethiopianorthodox.org/ በኢትዮጵያ ርትዕት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን] <br> በቤዛንቲያን ቤተክርስቲያን <br> በ[[ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን]]<br>በኮፕት ቤተክርስቲያን <br> በምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን|label8=የሚታወቁት|data8=በእግዚአብሔር ኃይል [[ገብርኤል (መልዐክ)|በቅዱስ ገብርኤል]] አማካኝነት እንደ እሳት ከፈላ ውሀ ውስጥ ያለምንም ጉዳት መውጣት ። |captionstyle=
|header9=}}
'''ቅዱስ ቂርቆስ''' (በእንግሊዘኛ :[[:en:Cyricus and Julitta|Cyricus]]) (በአራማይክ : ܡܪܝ ܩܘܪܝܩܘܣ ܣܗܕܐ Mar Quriaqos Sahada ፤ በተጨማሪ Quiricus Cyriacus Quiriac) ሀገሩ ሮም አንጌቤን ነው ። አባቱ ቆዝሞስ ይባላል ። እናቱ ቅድስት እያሉጣ (በእንግሊዘኛ : [[:en:Cyricus and Julitta|Julitta]]) (በግሪክ: ουλίττα) (በአራማይክ ܝܘܠܝܛܐ, : Yolitha) በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች ። እኒህ ሁለት ሰማዕታት [[ማርያም|የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናቸው።]]
የሚታወቁበትም ታሪካቸው እንደሚከተለው ነው ።
ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ፳ኛው ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክኒያት "የጣዖታት ቤቶች ሁሉ ይከፈቱ ፣ ቤተክርስቲያኖች ሁሉ ይዘጉ" ብሎ በ፫፻፫ ዓ ም አወጀ ። በዚህ ጊዜ እኩሌቶቹ ተሰደዱ ቅድስት እያሉጣም ልጇ የ፫ ዓመት ሕፃን ነበረና ለርሱ ብላ ከሁለት አገልጋዮችዋ ጋር ሆና ወደ ኢቆንዮን ሸሸች ።
የዚችም ሀገር ክርስቲያኖች የባሰ ስቃይ ውስጥ ነበሩ ። መስፍነ ብሔሩ እስክንድሮስም ፣ ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ አላት ። እሷም ዓይን እያለው የማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች ። አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት ። እስኪ ይህንን ሕፃን ጠይቀው አለችው ። አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው ። መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ፣ ራሳቸውን እንኳን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም አለው ። እንዲህም በመለሰለት ጊዜ ተበሳጭቶ በብረት ጋን ውሀ አፍልታቹህ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው አለ ታዛዦቹም በብረት ጋን ውሀ አፈሉ ድምፁም እንደ ክረምት ነጎድጉዋድ ፵፪ ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር ።
ሊከቷቸውም ሲወስዱዋቸው እያሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ቂርቆስ ግን ፍርሀቷን አርቅላት እያለ ይጸልይላት እሷንም <blockquote>"ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ በዚያውስ ላይ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላካችን እኛንስ ያድነን የለምን" </blockquote> እያለ እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ከዚህም በኋላ እሷም ጨክና በፍፁም ልብ ሆነው ተያይዘው ከፈላው ውኃ ውስጥ ገብተዋል ።"
በዚህም ጊዜም ከዐላውያን ነገሥታት ከዐላውያን መናፍስት ቀርበው የመሰከሩለት በስሙ መከራ የተቀበሉለት [[ኢየሱስ|ጌታ መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ]] [[ገብርኤል (መልዐክ)|ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልን]] ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል ።
በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይለበለብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው አንገታቸውን ለስለት ሰጥተው በሰማዕትነት ዐርፈዋል ።
[[ስዕል:የቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እያሉጣ ሰማዕትነት.jpeg|250px|thumb|እውነት ተናግረው ፃድቃን ሰማዕትነታቸውን እንደተጎናጸፉ]]
ከመዝገበ ታሪክ
{{መደብ:ክርስትና}}
mis4hjmiovucwcmtu7zrgqj7hesbddl