የኢትዮጵያ አየር መንገድ

ከWikipedia

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ድርጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ሊቀ መንበር አቶ ስዩም መስፍን
ዋና አስፈጻሚ ባለ ሥልጣን አቶ ግርማ ዋቄ
ማእከላዊ ጣቢያ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ
የሠራትኞች ብዛት 4705 (ሰኔ 2006 እ.ኤ.አ)
የመንገደኞች ብዛት (በዓመት) 1,762,900 (እስከ ሰኔ 2006 እ.ኤ.አ)
የመንገደኛ አውሮፕላኖች 10 ቦይንግ 767; 6 ቦይንግ 757፤ 6 ቦይንግ 737፤ 5 ፎከር 50፤ 2 ደ ሃቪላንድ
የጭነት አውሮፕላኖች 2ቦይንግ 757፤ 1 ኤ.ኤን 12
ድህረ ገጽ http://www.ethiopianairlines.com


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መሥሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ የኾነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አየር መንገድ ድርጅት ነው። አየር መንገዱ ከቀድሞው ትራንስ ወርልድ ኤየርዌይስ/ Transworld Airways (TWA) ጋር በጋራ የተመሠረተ ሲሆን አስተዳደሩ በአሜሪካኖች እጅ ነበር፤ ድርጅቱ እ.ኤ.አ 30th December 1945 ተመሥርቶ ለመጀሜሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ በረራውን እ.ኤ.አ April 8, 1946 ከአዲስ አበባ ካይሮ አከናወነ። አየር መንገዱ ሲመሰረት ከአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የተገዙ በሁለተኛው ዓለም ጦርነት ያገለገሉ አምስት ዲ.ሲ. 3 (DC 3-C47) አውሮፕላኖች ነበሩት። በዓለም ዙሪያ በአፍሪካ፤ በእስያ፤ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ክፍለ አህጉራት ወደ 50 የመንገዴኛና የጭነት አገልግሎት ሲሰጥ፤ በሀገር ውስጥ ደግሞ በአሁኑ ጊዜ 16 መድረሻዎችን ያገለግላል። ዋና የጣቢያው ማዕከል በአዲስ አበባ የሚገኘው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የራሱ አውሮፕላን አብራሪ ማሰልጠኛ ትምሕርት ቤት ሲኖረው የግል አብራሪ እና የንግድ አውሮፕላን አብራሪ ፈቃድ በመስጠት የሀገር ልጆችንም ሆነ የውጭ ዜጎችን በማሰልጠን እስከ አርባ ዓመት ልምምድ አለው። እንዲሁም ለብዙ የአፍሪካ ሀገር ብሔራዊ አየር መንገዶችና የግል አውሮፕላኖች የጥገና አገልግሎት ይሰጣል።