ደበበ እሸቱ

ከWikipedia

ደበበ እሸቱ (1936 ዓ.ም. ተወልደው) ስመ ጥር ተዋናይ ሲሆኑ በእሁኑ ግዜ የቅንጅት ቃል አቀባይ ሆነዋል። ከፊልሞቻቸው ሚናዎች መሃል በአለም ከሁሉ የታወቀው በShaft in Africa (1973 እ.ኤ.አ.) እንደ 'ዋሳ' ነበረ።

ትምህርታቸውን በተፈሪ መኮነን ትምህርት ቤት ጨርሰው ወደ ደብረ ብርሃን አስተማሪዎች ኮሌጅ ገቡ። ነገር ግን በ1952 ዓ.ም. በመንግስቱ ነዋይ በደረሰው ሁከት ወቅት ትምህርት አቋርጠው ወደ ኢሉባቦር ሸሹና ከ1 አመት በላይ እዚያ ቆዩ።

መጀመርያ በቴያትር የታዩ በመንግስቱ ለማ በተጻፈው Marriage by Abduction ሲሆን ከዚያ በአንዳንድ እንግሊዝኛ ትርኢት ('Marriage of Unequals', 'Waiting for Godot') እንዲሁም በራዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ተጫወቱ። ሥራቸው ደግሞ በኢትዮጵያ አየር ኅይል ውስጥ ነበረ።

ከዚያ በኋላ በሀንጋሪ አገር ከወጋየሁ ነጋቱ ጋራ ቴያትር አጠኑና ወደ አገራቸው ተመልሰው ደበበ 'ንጉሥ ሄሮድያስ' በተባለ ድራማ የአርእስቱ ሚና አጫወቱ።

ከዚህ በላይ በሀገር ፍቅር ቴያትር እንደ ዋነኛ ዳይረክተር፣ በመረጃ ሚኒስቴር እንደ ጋዜጠኛ፣ እና ከስብሃት ገብረ እግዚአብሄር ጋር በቁም ነገር መጽሔት እንደ አዘጋጅ አገልግለዋል።

ለአፍሪካዊ ቴያትር ስላደረጉት አስተዋጽኦአቸው ሽልማት በ1991 ዓ.ም. ከቦስቶን ከተማ እና በ1994 ከአትላንታ ከተማ በአሜሪካ ተቀበሉ። ከዚህ በላይ በ1994 ዓ.ም. የጣይቱ ሽልማት ተቀባይ ነበሩ።

የ30 አመት ሚስታቸው ው/ሮ አልማዝ እና እሳቸው 4 ልጆች አሏቸውና ከሴት ልጆቹም 2ቱ በ1 ቀን ውስጥ በ1995 ዓ.ም. ለባሎቻቸው ተዳሩ።

በቅርብ ግዜ ከፖለቲካ ነክ ሚናቸው የተነሣ እቶ ደበበ ከ1998 እስከ 1999 ዓ.ም. ድረስ የቃላቲ እስራኛ ነበሩ።

[ለማስተካከል] ፊልሞች

  • Gouma (1975)
  • Zelda (1974)
  • Shaft in Africa (1973) - Wassa
  • Una Stagione all'inferno (1970)
  • The Sailor from Gibraltar (1967)