ከWikipedia
ለአለም ጽሕፈቶች ወላጅ ሆነው የሚታስቡ 2 ተመሳሳይ ጽሕፈቶች ተገኝተዋል፣ እነሱም "ጥንታዊ የሲና ጽሕፈት"ና "የዋዲ ኤል ሖል ጽሕፈት" ይባላሉ። "ዋዲ ኤል ሖል" በ1999 እ.ኤ.አ. በግብፅ ተገኝቶ ዕድሜው ከክ.በ. 1800 ዓመት ሲገመት የጥንታዊ ሲና ጽሕፈት በ1904 እ.ኤ.ኣ. በደብረ ሲና በኩል ተገኝቶ ከክ.በ. 1500 ዓመት የተጻፈ ይታመናል።
==ጥንታዊ የሲና ጽሕፈት==ሳሃለነ ቅደሰት ሰሃለነ ቅድስት ሳሃለነ ቅድስት።ከሲና ልሣነ ምድር በላይ አሁን ለዚህ ጽሕፈት በርካታ ምሳሌዎች በከነዓን (የዛሬው እስራኤል) ደግሞ ተገኝተዋል። በተለይ የሚታወቀው ደብረ ሲና አጠገብ ካለ አረንጓዴ ፈርጥ ማዕድን ቦታ ነው። ነገር ግን አሁን 100 አመት ከተገኘ በኋላ የቋንቋ ሊቃውንት ስለ ተቀረጹት ቃላት ትርጉም በሙሉ እርግጠኛ አይደሉም።ያንጋደደ ጽሕፈት
[ለማስተካከል] የዋዲ ኤል ሖል ጽሕፈት
ይህ ጽሕፈት በግብጽ መካከል ተግኝቶ በሴማዊ ሠራተኞች እንደ ተቀረጸ ይታስባል። የፊደሎቹ ቅርጽ ለግብጽኛ ስዕል ጽሕፈት (ሀይሮግሊፍ) ተመሳሳይ ነው። ለጥንታዊ ሲና ጽሕፈት ደግሞ ይመሳሰላል። ስለዚህ ሰራተኞቹ ስእሎቹን ተበድረው ለራሳቸው ቋንቋ የሚስማማ ድምጽ እንደ ሰጡት ይታመናል።
ለምሳሌ በጥንታዊ ግብጽኛ ቋንቋ እባብ ማለት "ጀት" ነበር። ስለዚህ በግብጽ ጽሕፈት የእባብ ስዐል "ጀ" ለማመልከት ጠቀመ። ነገር ግን በግብጽ ለኖሩት ሴማዊ ሰራተኞችና አገልጋዮች በቋንቋቸው የእባብ ስም በ "ነ" ስለ ጀመረ የእባብ ምልክት ከ "ጀ" ወደ "ነ" ተዛወረ።
እንዲሁም ውሃ በግብጽኛ "ነት" ስለነበር የውሃ ምልክት በድምጹ "ነ" ለመጻፍ ይጠቅም ነበር። ደግሞ ለሴማውያን የውሀ ስም በ "መ" ስለጀመረ (ማይ) የውሀ ምልክት በጽህፈታቸው "ነ" ሳይሆን "መ" እንዲሆን ተደረገ።