ጅማ

From Wikipedia

ጅማ በምዕራብ ኢትዮጵያ ካሉት ከተማ በስፋት ያላቀች ከተማ ናት። በኦሮሚያ ክልል በጅማ ዞነ ስተገኝ በላቲቱድና ሎንጂቱደ 7°40′N 36°50′E ላይ ናት። የቀድሞው ከፋ ክፍለ ሃገር ዋና ከተማ ሆና አገልግላለች።

የብሔራዊ የስታትስቲክ ባለስልጣን በ1998፥ የ159,009 ሕዝብ መኖሪያ ከነሱም መካከል 80,897 ውንዶችና 78,112 ሴቶች መሆችውን ተምኗል። ሄርበርት ሉዊስ በ1950ዎቺ የምእራብና ደቡብ ኢትዮጵያ አንጋፋ ገበያ ሲላት በአንድ የበጋ ቀን እስክ ሰላሳ ሺህ ሰው ትስብ እንደነበር ይናገራል። በጅማ የቀድሞ የጅማ ንግስታ የገነቧችው አንዳንድ ቅሪቶች እንደ የአባ ጅፋር ቤተ መንግስት ዛሬ ይታያሉ። ከተማዋ የአንድ ሙሲየም የጅማ ዩኒቨርስቲ የተለያዩ ገበያዎችና የአንድ ኤርፖርት መቀመጫ ናት።