ሹቡር

From Wikipedia

ሹቡር (ሱመርኛ፡ ሱቢር፣ ሱባር፣ ሹባር፣ ሹቡር፤ አካድኛ፦ ሱባርቱ፣ ሹባርቱም፣ ሱባርቱም፣ ሹባሪ) ከሰናዖር ወደ ስሜን በጤግሮስ ወንዝ ላይ የተቀመጠ አገር ነበረ። ይህም ስም በጥንታዊ አማርና ደብዳቤዎችና በኡጋሪት መዝገቦች 'ሽብር' ተጽፎ ተገኝቷል።

ከሁሉ ጥንታዊ በሆነ ዘመን፣ ከሰናዖር (ሱመር) ዙሪያ ሌሎቹ '4 ሩቦች' 'ማርቱ' (አሞራውያን)፣ 'ሱባርቱ'፣ ኤላምና 'ኡሪ -ኪ' (አካድ) ነበሩ።

የአካድ ንጉስ 1 ሳርጎን በሱባር ላይ ዘመቻ ያድርግ ነበርማ ናራም-ሲን ከገዛቸው አገራት መካከል ቆጠሩት። የኢሲን ንጉስ ኢሽቢ-ኤራ እና የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ደግሞ በሱባር ላይ እንዳሸነፉት ይታመናል።

በአዲሱ የባቢሎን መንግሥት ዘመን በናቦፖላሣር፣ በ2 ናቡከደነጾርና በናቡናኢድ ዘመናት 'ሱባርቱ' ለአሦር በጠቅላላ ዘይቤ ነበር። እንኳን በፋርስ ንጉስ በካምቦሥሥ ዘመን 'ሱባርቱ' የሚለው ስም ይጠቀም ነበር።

ከሊቃውንት ብዙዎች 'ሱባርቱ' ለአሦር ቤት ጥንታዊ ስም እንደ ነበር ይቀበላሉ። ሆኖም ከዚያ አገር ትንሽ ወደ ምሥራቅ፣ ስሜን ወይም ምዕራብ እንደ ነበር የሚሉ ሃሳቦች አሉ። አንዳንድ ጸሐፊ ከሆራውያንም ግኙነት እንደነበራቸው ብሏል።

በሌሎች ቋንቋዎች