ድንት

From Wikipedia

ደ ዱ ዲ ዳ ዴ ድ ዶ ዷ



አቡጊዳ ታሪክ

ድንት (ወይም ድልት) በአቡጊዳ ተራ አራተኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓን በአራማያና በዕብራይስጥ በሶርያም ፊደሎች አራተኛው ፊደል "ዳሌት" ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል "ዳል" ተብሎ በ"አብጃድ" ተራ 4ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 8ኛው ነው።) በግሪክም 4ኛው ፊደል "ዴልታ" ይባላል። በነዚህ ቋንቋዎች ሁሉ አጠራሩ "ድ" ነው።

አማርኛ ደግሞ "ጀ ጁ ጂ ጃ ጄ ጅ ጆ" ከ"ደ..." ትንሽ ተቀይሯል።

[ለማስተካከል] ታሪክ

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
O31
Image:Proto-semiticD-01.pngImage:Proto-semiticD-02.png Image:Himjar dal.PNG


የድንት መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ ወይም የደጅ ወይም የዓሣ ስዕል መስለ። ለደጅ ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ "ዐእ" ነበር።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ድንት ድንት ד ድንት


የከነዓን "ዳሌት" እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ "ዳሌት" የአረብኛም "ዳል" ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት "ዴልታ" (Δ δ) አባት ሆነ፤ እሱም የላቲን አልፋቤት (D d) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Д, д) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ"ድንት" ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (አራት) ከግሪኩ Δ በመወሰዱ እሱም የ"ደ" ዘመድ ነው።

በሌሎች ቋንቋዎች