ማርሽ ተፈሪ

From Wikipedia

ማርሽ ተፈሪ ከ1923 ዓ.ም. እስከ 1967 ድረስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር ነበር።

ከቮርክ ናልባንዲያን የንጉስ ጓድ መሪ በ1918 ሙዚቃውን ተቃኘ። 40 አርሜናውያን ('አርባ ልጆች') ከቱርክ እልቂት አምልጠው እስከ ኢየሩሳሌም ገዳም ድረስ ሸሽተው ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ አመጧቸውና በኢትዮጵያ ኖሩ።

ቃላቱን የተቃኘው ዮፍትሄ ንጉሤ ነው።

[ለማስተካከል] ቃላት

ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ
በአምላክሽ ኃይል በንጉሥሽ
ተባብረዋልና አርበኞችሽ
አይነካም ከቶ ነጻነትሽ
ብርቱ ናቸው ተራሮችሽ
አትፈሪም ከጠላቶችሽ
ድል አድራጊው ንጉሳችን
ይኑርልን ለክብራችን

[ለማስተካከል] ውጭ መያያዣዎች

በሌሎች ቋንቋዎች