የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን

From Wikipedia

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘ ምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ነው። እስከ 1951 ዓ.ም. ድረስ የቅብጥ ቤተ ክርስቲያን ክፍል ነበር። በዚያ አመት ግን የቅብጥ አቡና 6ኛ ቂርሎስ ለኢትዮጵያ የራሱን አቡነ እንዲኖሩት ፈቀዱለት። ከቅኝ ግዛት ዘመን አስቀድሞ እና ከሳሃራ በረሃ ደቡብ የሚገኘው አንድያ ቤተ ክርስቲያን እሱ ነው። ወደ 40-45 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው።

ይዞታ

[ለማስተካከል] መሠረቶች

"ተዋሕዶ" ማለት ከልሣነ ግእዝ ተለቅቆ ትርጒሙም "አንድ ሆኖ" ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል "ታውሒድ" ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን ያለው ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል። በምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ"ሰብዓዊ" እና በ"መለኮታዊ" ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።

በ443 ዓ.ም. የሮማ ንጉስ ያሰበሰበው የኬልቄዶን ጉባኤ ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርዮች እንደነበረው አዋጀ። የእስከንድርያ የአንጾኪያና የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ግን ይህን የሮማ ጳጳስ ትምህርት ለመቀበል ስላልቻሉ፡ የሮማ ጳጳስ ወዲያው አወገዛቸውና መከፋፈል ሆነ። ከሮማ መንግሥት ጠረፎች ውጭ የነበሩት አብያተ ክርስትያናት በተለይ አዲሱን ትምህርት እንዲቀበሉ ምንም ግዴታ ስላልነበረባቸው እነዚህ አብያተ ክርስትያናት ዛሬ የአርሜኒያ፣ የሕንደኬ፣ የግብጽ፣ የሶርያ፤ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት ናቸው።

የቤተክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ ቅዱስ ፊልጶስ መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ 8)፦

«እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር...»

በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቷቸው ከዚያው ጃንደረባው ተጠመቁ። ንግሥት ግርሳሞት ህንደኬ 7ኛ ከ34 ዓ.ም. እስከ 44 ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።

በ4ኛ ምዕተ ዘመን በንጉስ ኤዛና ዘመን በፍሬምንጦስ አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምንጦስ በኢትዮጵያ 'አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን' ተብለው ይታወቃሉ። ወጣት ሆነው ከወንድማቸው ከአይዲዝዮስ ጋራ መርከባቸው በመውጅ ሰብሮባቸው በኤርትራ ከደረሱ በኋላ፣ ወደ ንጉሡም ግቢ አመጡዋቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበት ደረጃ አገኙ። ንጉስ ኤዛና ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምንጦስን ለኢትዮጵያ አቡነ እንዲሾም ለመጠይቅ ወደ እስክንድርያ ላኩዋቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ አቴናስዮስ ፍሬምንጦስን እራሳቸውን ሾመው ልከዋል። ከዚያ እስከ 1951 ዓ.ም. ድረስ የኢትዮጵያ አቡነ የተመረጡት ከቄብጦች መኻል ነበር።

እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት አልቀረም። ጽሐፊው አቡ ሳሊኅ በ12ኛ መቶ ዘመን እንደ ገለጸው ፓትርያርኩ በየዓመቱ 2 ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። 67ኛው ፓትረያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተክርስቲያን ሥራዓት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ1431 ዓ.ም. በአጼ ዘርዕ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከ1 ፈረንሳያዊ ጐባኝ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስላነጋገሩ አንድ ተልእኮ ወደ ሮማ ተላከ።

[ለማስተካከል] በቅርብ ጊዜ

[ለማስተካከል] ልዩ ባሕርይ

[ለማስተካከል] የሚቀበሉ ቅዱሳን መጻሕፍት

ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ (ከነዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ሁሉ) በመቀበል ብቸኛ ሃገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቅዱሳት መጻህፍት ቁጥራቸው 81 ሲሆን እነዚህም 35 የሐዲስ ኪዳን መጻህፍትና 46 የብሉይ ኪዳን መጻህፍት ናቸው። ይህ የቅዱሳት መጻህፍት ቁጥር በቀኖና አበው 318ቱ ሊቃውንት በኒቂያ ገባኤ ተደንግገዋል።

[ለማስተካከል] ልሳነ ቅዳሴና ልሳነ ስብከት

[ለማስተካከል] ሥነ ሕንፃ

ቤተ ጊዮርጊስ፣ ላሊበላ
Enlarge
ቤተ ጊዮርጊስ፣ ላሊበላ

[ለማስተካከል] ታቦት

መድህኒታችን አየሱስ ክርስቶስ ንጥው የወነ የጊታችን አምሳል ነው ታቦታ:

[ለማስተካከል] ሕገ ኦሪት