የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
From Wikipedia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነው። እስከ 1951 ዓ.ም. ድረስ የቅብጥ ቤተ ክርስቲያን ክፍል ነበር። በዚያ አመት ግን የቅብጥ አቡና 6ኛ ቂርሎስ ለኢትዮጵያ የራሱን አቡነ እንዲኖሩት ፈቀዱለት። ከቅኝ ግዛት ዘመን አስቀድሞ እና ከሳሃራ በረሃ ደቡብ የሚገኘው አንድያ ቤተ ክርስቲያን እሱ ነው። ወደ 40-45 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው።
ይዞታ |
[ለማስተካከል] በታሪክ
[ለማስተካከል] መሠረቶች
"ተዋሕዶ" ማለት ከልሣነ ግእዝ ተለቅቆ ትርጒሙም "አንድ ሆኖ" ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል "ታውሒድ" ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን ያለው ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ"ሰብዓዊ" እና በ"መለኮታዊ" ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።
በ443 ዓ.ም. የሮማ ንጉስ ያሰበሰበው የኬልቄዶን ጉባኤ ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርዮች እንደነበሩት አዋጀ። የእስከንድርያ የአንጾኪያና የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ግን ይህን የሮማ ጳጳስ ትምህርት ለመቀበል ስላልቻሉ፡ የሮማ ጳጳስ ወዲያው አወገዛቸውና መከፋፈል ሆነ። ከሮማ መንግሥት ጠረፎች ውጭ የነበሩት አብያተ ክርስትያናት በተለይ አዲሱን ትምህርት እንዲቀበሉ ምንም ግዴታ ስላልነበረባቸው እነዚህ አብያተ ክርስትያናት ዛሬ የአርሜኒያ፣ የሕንደኬ፣ የግብጽ፣ የሶርያ፤ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት ናቸው።
የቤተክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ ቅዱስ ፊልጶስ መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ 8)፦
- «እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር...»
በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቷቸው ከዚያው ጃንደረባው ተጠመቁ። ንግሥት ግርሳሞት ህንደኬ 7ኛ ከ34 ዓ.ም. እስከ 44 ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።
በ4ኛ ምዕተ ዘመን በንጉስ ኤዛና ዘመን በፍሬምንጦስ አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምንጦስ በኢትዮጵያ 'አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን' ተብለው ይታወቃሉ። ወጣት ሆነው ከወንድማቸው ከአይዲዝዮስ ጋራ መርከባቸው በመውጅ ሰብሮባቸው በኤርትራ ከደረሱ በኋላ፣ ወደ ንጉሡም ግቢ አመጡዋቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበት ደረጃ አገኙ። ንጉስ ኤዛና ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምንጦስን ለኢትዮጵያ አቡነ እንዲሾም ለመጠይቅ ወደ እስክንድርያ ላኩዋቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ አቴናስዮስ ፍሬምንጦስን እራሳቸውን ሾመው ልከዋል። ከዚያ እስከ 1951 ዓ.ም. ድረስ የኢትዮጵያ አቡነ የተመረጡት ከቄብጦች መኻል ነበር።
[ለማስተካከል] መካከለኛ ዘመን
እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት ተቸገረ። ጽሐፊው አቡ ሳሊኅ በ12ኛ መቶ ዘመን እንደ ገለጸው፣ ፓትርያርኩ በየዓመቱ 2 ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። 67ኛው ፓትረያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተክርስቲያን ሥራዓት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ1431 ዓ.ም. በአጼ ዘርዕ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከ1 ፈረንሳያዊ ጐባኝ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስላነጋገሩ አንድ ተልእኮ ወደ ሮማ ተላከ።
በ1500 ዓ.ም. ደግሞ ኢትዮጵያ ከአዳል ጋር ስትታገል ማቴዎስ የተባለ አንድ አርሜናዊ ወደ ፖርቱጋል ተልኮ የፖርቱጋል ንጉስ እርዳታ ለመነ። ስለዚህ በ1512 ዓ.ም. የፖርቱጋል ሚሲዮን በኢትዮጵያ ደረሰ። በሚከተለው ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋል ኢየሱሳውያን የተባሉ ሚሲዮኖች ቤተ መንግሥቱን ወደ ሮማ ካቶሊክ ሃይማኖት እንዲዞሩ በብዙ ጣሩ። በመጨረሻ በ1617 ዓ.ም. ንጉስ ሱስንዮስ ወደ ሮማ ፓፓ ተሰለሙ። ነገር ግን የሮማ ሃይማኖት በተዋህዶ ፈንታ ይፋዊ መሆኑን ሕዝቡ በጣም አልወደደምና በ1625 ሱስንዮስ ዘውዳቸውን ለልጃቸው ለፋሲላድስ እንዲሰጡ ተደረጉ። ፋሲላድስ ወዲያው አገሩን ወደ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መለሱ። ከዚህ በላይ በ1626 ፋሲላደስ ኢየሱሳውያን አገሩን ለቅቀው እንዲሄዱ አዘዙ። በ1658 ዓ.ም. መጻሕፍታቸውን ደግሞ አስቃጠሉ።
[ለማስተካከል] በቅርብ ጊዜ
[ለማስተካከል] ልዩ ባሕርይ
[ለማስተካከል] የሚቀበሉ ቅዱሳን መጻሕፍት
ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ (ከነዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ሁሉ) በመቀበል ብቸኛ ሃገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቅዱሳት መጻህፍት ቁጥራቸው 81 ሲሆን እነዚህም 35 የሐዲስ ኪዳን መጻህፍትና 46 የብሉይ ኪዳን መጻህፍት ናቸው። ይህ የቅዱሳት መጻህፍት ቁጥር በቀኖና አበው 318ቱ ሊቃውንት በኒቂያ ገባኤ ተደንግገዋል።
[ለማስተካከል] ልሳነ ቅዳሴና ልሳነ ስብከት
[ለማስተካከል] ሥነ ሕንፃ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሥነ ሕንፃ የቤተክርስቲያኖ ትውፊታዊ የሥነ ሕንጻ ጥበብዋ አምስት ዐይነት ነው ። እነርሱም ክብ ፤ መስቀል ቅርፅ ፤ ዋሻ ፤ ፍልፍል እና ስቀልማ ናቸው ። ክብ ሕንጻ አብያተክርስቲያናት በብዛት በገጠሪቷ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን ፤ መስቀል ቅርጽ ያላቸው ደግሞ በከተማ አካባቢ ይገኛሉ። ዋሻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በተራራማ አካባቢዎች ሢገኙ ፤ ፍልፍል አብያተክርስቲያናት ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍለው የተዘጋጁ ናቸው። ሰቀልማ የሚባለው እንደ ጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ ያሉ አብያተክርስቲያናት ናቸው ።
[ለማስተካከል] ታቦት
መድህኒታችን አየሱስ ክርስቶስ ንጥው የወነ የጊታችን አምሳል ነው ታቦታ: