መለስ ዜናዊ
From Wikipedia
መለሰ ዜናዊ (የትውልድ ስማቸው ለገሠ ዜናዊ አስረስ) ኢትዮጵያ የፖለቲካ ሰው ናቸው። በአድዋ ትግራይ በ(ሚያዝያ 30 ቀን 1947 ዓ.ም. ተወለዱ። ከ1987 አንስተው በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን በከፍተኛው የአመራር ቦታ ላይ ናቸው። የኢህአዴግና የሕውሓት ፕሬዚዳንት በመሆን ኢህአዴግ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ይታወቃሉ።
ኣቶ መለስ ዜናዊ ኣባታቸው የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ በእናታቸው በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ናቸው፡፡
ይዞታ |
[ለማስተካከል] ወደ ስልጣን አመጣጥ
ሕውሓት የኮሎኔል መንግስቱ ኅይለ ማርያምን አምባ ገነናዊ መንግስት በትጥቅ ሲታገሉ ከነበሩ ድርጅቶች አንዱ ነው። አቶ መለስ የሕወሓት አመራር ኮሚቴ መሪ ሆነው በ1971 ተመረጡ ቀጥሎም በ1975 የዋናው መሪዎች ቡድን አለቃ ሆኑ። የደርግ መንግስት ከወደቀም ጀምሮ የሕውሓትና የኢህአዴግ ሊቀ መንበርም ናቸው። ኢህአዴግ የአራቱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግራይና የደቡብ ሀዝቦች ብሔር ውህደት ነው። ወደ ስልጣን ሲመጡ በጊዜው ላቋቋሙት ጊዜያዊ መንግስት ፕረዚዳንት ሆነው ካገለገሉ በሗላ 1985 ለመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው ተመረጡ። በጊዜው የፕረዚደንትነቱን ቦታ የተረከቡት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ናችው። በመቀጠልም አቶ መለስ ከባድ ውዝግብ ባስነሳው የ1997 ግንቦት ምርጫ አሸናፊ ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ በስልጣን ላይ ይገኛሉ።
[ለማስተካከል] የኢህአዴግ ደጋፊዎች
በአምባ ገነኑ ደርግ ስር ተጨቁኖ ለነበረው ድሃ ኢትዮጵያዊ የኢህአደግ ወደ ስልጣን መምጣት ከ«የምስራች» ውጭ ሌላ ነገር አልነበረም። ከዚህም የተነሳ ኢህአዴግ ይህ ነው የተባለ ተቃውሞ አልገጠመውም። ከዚህም በተጨማሪ የአረብና የምዕራባውያን መንግስታት ከጎንህ አለን በማለት በብዙ ትግል ስልጣን የተቆናጠጠውን ኢህአደግን በሁለት እግሩ አንዲቆም አስችለውታል።
[ለማስተካከል] የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች
ምንም እንኳ በደርግ የግፍ አገዛዝ የተማረረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ኢህአዴግን ለመቀበል ወደ ኋላ ባይልም ውሎ ሲያድር ግን በኢህአዴግ የአገር ውስጥ ፖሊሲ መከፋቱ አልቀረም። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ብሎ ራሱን የስየመው ቡድን ከኢህአዴግ ጋር መጣላቱን ለማብስር የቀደምው አልነበረም። ጠ/ም መለስ የኤርትራን የመገንጠል ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር መፍቀዳቸው ብዙ ተቃውሞን አስነስቶባቸዋል። ሁሉም በቋንቋው የተሰኘው ፖሊሲያችውም በብዙዎች ዘንድ በጥርጣሬ ይታያል። በዚሀም ምክንያት በሀገርና ከሀገር ውጭ በተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፎች ተካይዶባቸዋል። ለውጥ ይፍልጋል
[ለማስተካከል] የሽግግር መንግስታቸው
የመንግስቱ ኃይለ ማርያምን መሸነፍ ተከትሎ የሐምሌው ስምምነት ተደረገ። ይህም ብዙ ብሔር የተሳተፈበትና ቀድሞ ያልታየ ነበር። ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ብቻ ጎልቶ የታየበት ስለነበር ብዙኅኑን ያስደሰተ አልነበረም ስለሆነም ከትችትና ከተቃውሞ አላመለጠም።