ግዕዝ

From Wikipedia

ኦሪት ዘፍጥረት 29 በግዕዝ መጽሐፍ ቅዱስ
ኦሪት ዘፍጥረት 29 በግዕዝ መጽሐፍ ቅዱስ

ግዕዝ በአፍሪካ ቀንድ በኢትዮጵያና በኤርትራ በጥንት የተናገረ ቋንቋ ነው። በአክሱም መንግሥትና በኢትዮጵያ መንግሥት መደበኛ ቋንቋ ነበር። ዛሬ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥነ-ስርዓት እንዲሁም በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እና በቤተ እስራኤል ሥነ-ስርዓቶች እስከ ዛሬ ድረስ ይሰማል።

ቋንቋው የሴማዊ ቋንቋዎች አባል እየሆነ በደቡብ ሴማዊ ቅርንጫፍ ውስጥ ይከተታል። ደቡብ ሴማዊ በመባሉ ግዕዝ የሣባ ቋንቋ ቅርብ ዘመድ ነው። ግዕዝ የተጻፈው በግዕዝ ፊደል አቡጊዳ ነው። ይህም ፊደል ደግሞ ዛሬ ለአማርኛ ለትግርኛ ለሌሎችም ቋንቋዎች ይጠቀማል።

በግዕዝ ጽሕፈት 26 ፊደላት ብቻ ይጠቀሙ ነበር፤ እነርሱም፦

፣ ሰ፣ ቀ፣ ፣ ተ፤ ኀ፣ ነ፤ ፣ ከ፣ ወ፣ ዐ፣ ዘ፣ የ፣ ደ፣ ፣ ጠ፣ ጰ፣ ጸ፣ ፀ፣ ፈ፣ ፐ

ናቸው።

ሊቁ ሪቻርድ ፓንኩርስት እንደሚጽፍ፣ አንድ ተማሪ በመጀመርያው አመት ፊደሉን ከተማረ በኋለ፣ በሚከተለው አመት መጀመሪያይቱ የሐዋርያው የዮሐንስ መልእክትን ከአዲስ ኪዳን በግዕዝ ከትዝታ ለመጻፍ መማር ነበረበት። በሦስተኛው ደረጃ የሐዋርያት ሥራ በአራተኛውም መዝሙረ ዳዊት በግዕዝ ማስታወስ ነበረበት። ይህንን ከጨረሰ ታላቅ ግብዣ ተደረገና ልጁ ጸሐፊ ይሆን ነበር።

በብሪቲሽ ላይብሬሪ (የእንግሊዝ አገር ብሔራዊ በተ መጻሕፍት) ውስጥ 800 የሚያሕሉ የድሮ ግዕዝ ብራናዎች ይኖሩበታል።

[ለማስተካከል] ምሳሌ

«ቃለ፡ በረከት፡ ዘሄኖክ፡ ዘከመ፡ ባረከ፡ ኅሩያነ፡ ወጻድቃነ፡ እለ፡ ሀለው፡ ይኩኑ፡ በዕለተ፡ ምንዳቤ፡ ለአሰስሎ፡ ኲሉ፡ እኩያን፡ ወረሲዓን።» (መጽሐፈ ሄኖክ 1፡1)

ሄኖክ መጀመርያ ቃሎች በጽሕፈት የጻፈ እንደ ነበር ስለሚባል፣ ይህ ቃል በማንኛውም የሰው ልጅ ቋንቋ ከሁሉ አስቀድሞ የተጻፈ መሆኑ በብዙዎች የኢትዮጵያ ሊቃውንት ይታመናል።

በሌሎች ቋንቋዎች