ሏንዳ

From Wikipedia

ሏንዳ (Luanda) የአንጎላ ዋና ከተማ ነው።

ሏንዳ በ1997 ዓ.ም.
ሏንዳ በ1997 ዓ.ም.

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር (1996 ዓ.ም.) 4.5 ሚሊዮን ሆኖ ይገመታል። ከተማው 08°50′ ደቡብ ኬክሮስ እና 13°15′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ከተማው በ1567 ዓ.ም. ሳን ፓውሎ (ቅዱስ ጳውሎስ) ዴ ሏንዳ ተብሎ በፖርቱጋል ሰዎች ተመሠረተ። ከ1619 ዓ.ም. ጀምሮ የአንጎላ መቀመጫ ሆኗል። ነገር ግን ከ1632 እስከ 1640 ዓ.ም. ድረስ የሆላንድ ሰዎች ይዘውት ስሙን ፎርት አርደንግቡርግ አሉት።