ዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን

From Wikipedia

«ይህ ገጽ ከእንግሊዝኛው በቀጥታ የተቀዳ ነው። ቀስ በቀስ ይተረጎማል በማለት ነው።»

ዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያንቤጂንግ ቻይና በ1909 ዓ.ም. የተመሠረተ ነፃ ቤተ ክርስቲያን ነው። በ6 አህጉር ላይ 1.5 ሚሊዮን የሚያሕሉ ምዕመናን አሉት። ቤተ ክርስቲያኑ በቻይና የወጣ ከጰንጤ እንቅስቃሴ የተነሣ ነው።

ይህ ቤተ ክርስቲያን ግን የሥላሴ ጽንሰ ሐሳብ አይቀበልምና «የኢየሱስ ስም ትምሀርት» ተከታዮች ናቸው።

ይዞታ

[ለማስተካከል] አምስቱ ዋና ትምህርቶች

የዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን 5 አይነተኛ ትምሀርቶች እንደሚከተል ናቸው፦

[ለማስተካከል] መንፈስ ቅዱስ

«መንግሥተ ሰማያትን የመውረሳችን ዋስትና መንፈስ ቅዱስ በመቀበል ነውና እሱም ባልታወቀ ልሳናት በመናገር ይገለጻል።»

[ለማስተካከል] ጥምቀት

«የውሃ ጥምቀት ለኃጥአት ስርየት ለተሐድሶ የሆነው ቁርባን ነው። ጥምቀቱ መደረግ ያለበት በተፈጥሮ ኗሪ ውኃ ለምሳሌ እንደ ወንዝ፣ ባሕር ወይም ምንጭ ውስጥ እንዲሆን ያስፈልጋል።

ከዚህ ቀድሞ የውኃ ጥምቀትና መንፈስ ቅዱስ የተቀበለው መጥምቅ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያጠምቀዋል። ተጠቃሚውም ራሱን አጎንብሶ ወደ ታች ሲመለከት በውኃ በሙሉ እንዲታጠብ ነው።»

[ለማስተካከል] እግር ማጠብ

«የግሮች ማጠብ ምስጢር ሰው ከጌታ ኢየሱስ ጋር ድርሻ እንዲኖረው ያስችለዋል። ደግሞ ፍቅር፣ ቅድስና፣ ትሕትና፣ ይቅርታ እና አገልግሎት እንደሚያስፈልጉት እንደ ዘወትር ማስታሰቢያ ያገለግላል።

የውኃ ጥምቀት የተቀበለ ሰው ሁሉ እግሮቹን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲታጠብ አለበት። በሚገባበት ጊዜ እርስ በርስ መታጣጠብ ሊሠራ ይችላል።»

[ለማስተካከል] ቅዱስ ቁርባን

«ቅዱስ ቁርባን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ መሞት የሚያከብረው ምስጢር ነው።

ዘላለማዊ ሕይወት እናገኝ ዘንድ በመጨረሻም ቀኝ እንነሣ ዘንድ፣ ከጌታችን ሥጋ ወደም ለማሳተፍ ከሱም ጋር ለመቈረብ ያስችለናል። ይኸው ቁርባን እስከሚቻል ድረስ ብዙ ጊዜ ይደረጋል። አንድ ቂጣ እና የወይን ጭማቂ ብቻ ይጠቀማል።»

[ለማስተካከል] የሰንበት ቀን

«የሰንበት ቀን፥ የሣምንቱ ሰባተኛ ቀን (ቅዳሜ) በእግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሠ ቅዱስ ቀን ነው። የእግዚአብሄርን ፍጥረትና መድኃኒት ለማስታወስና በሚመጣው ሕይወት የዘላለማዊ ዕረፍት ተስፋ ከማድረግ ጋራ በጌታ ጸጋ መሠረት ይከብራል።»

[ለማስተካከል] ተጨማሪ ትምህርቶች

በኋላ በ1980ዎቹ የዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን 10 መሠረታዊ እምነቶች ለመሆን በነዚህ 5 ዋና ትምህርቶች ላይ ሌሎች ተጨመሩ፦

[ለማስተካከል] ኢየሱስ

ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ሥጋ ሆኖ በመስቀል ላይ ስለ ኃጢአተኞች ቤዛነት የሞተው፣ በሦስተኛው ቀን ከሙታን የተነሣውና ወደ ሰማያት ያረገው ነው፤ እርሱ የሰው ልጆች ብቸኛ አዳኝና የሰማይና የምድር ፈጣሪ እንዲሁም እውነተኛ አምላክ ነው።

«Jesus Christ, the Word who became flesh, died on the cross for the redemption of sinners, ressurrected on the third day and ascended to heaven. He is the only Saviour of mankind, the Creator of the heavens and earth, and the only True God».

[ለማስተካከል] መጽሐፍ ቅዱስ

«The Holy Bible, consisting of the Old and New Testaments, is inspired by God, the only scriptural truth, and the standard for Christian living».


[ለማስተካከል] ደኀንነት

«ደኀንነት በእግዚአብሐር ጸጋ በእምነት ይሰጣል። ቅድስናን ለመከተል፣ እግዚአብሔርን ለማክበርና ሰዎችን ለመውደድ፤ አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ላይ መታመን አለባቸው።»

[ለማስተካከል] እውነተኛ ቤተክርስቲያን

«በ'ኋለኛ ዝናብ' ግዜ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተው እውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን የሃዋርያዊ ዘመን የታደሰ እውነተኛ ቤተ ክርስቲያን ነው።»

[ለማስተካከል] ዳግመኛ ምጣት

«የጌታው ዳግመኛ ምጽአት የሚደርሰው ዓለምን እንዲፈርድ ከሰማይ በወረደበት በመጨረሻ ቀን ነው። በዚያን ግዜ ጻድቃን የዘላለምን ሕይወት ይቀበላሉ፤ ክፉዎችም ለዘላለም ይኮነናሉ።»

በሌሎች ቋንቋዎች