ውክፔዲያ amwiki https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8B%E1%8A%93%E1%8B%8D_%E1%8C%88%E1%8C%BD MediaWiki 1.47.0-wmf.14 first-letter ፋይል ልዩ ውይይት አባል አባል ውይይት ውክፔዲያ ውክፔዲያ ውይይት ስዕል ስዕል ውይይት መልዕክት መልዕክት ውይይት መለጠፊያ መለጠፊያ ውይይት እርዳታ እርዳታ ውይይት መደብ መደብ ውይይት በር በር ውይይት TimedText TimedText talk ሞጁል ሞጁል ውይይት Event Event talk ደብረ ታቦር (ዓመት በዓል) 0 14322 394625 377382 2026-08-10T13:55:35Z ~2026-44110-12 60043 /* ዋቢ ምንጮች */ 394625 wikitext text/x-wiki '''ደብረ ታቦር''' ወይንም '''ቡሄ!''' በመላው ሀገራችን በየዓመቱ [[ነሐሴ 13|ነሐሴ ፲፫]] ቀን የሚከበር በዓል ሲሆን፤ [[የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን]] ከምታከብራቸው ዐቢይ (ዋና) በዓላት አንዱ ይሄ 'ደብረ ታቦር' (የቡሄ በዓል ነው።) == የበዓሉ መሠረት == የዚህ በዓል መሠረት የ[[ክርስቲያን]] እምነት ሲሆን፣ ደብረ ታቦር በ[[ግዕዝ]] የታቦር ተራራ ማለት ነው፡፡ የታቦር ተራራ የሚገኘው አሁን [[ፍልስጥኤም]] ታሪክ ማዛባት ነውር ነው ታቦር ተራራ(ሃር ታቦር) ተወደደም ተጠላ እስራኤል በምትባል ጥንታዊትና ዘመናዊት ሀገር በሰሜኑ የእስራኤል አገር ይገኛል:፡ ደብረ ታቦር ወይንም የታቦር ተራራ [[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደ[[ፀሐይ]] የበራበት ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ ይህ ቦታ ጌታ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው። <blockquote> [[የማቴዎስ ወንገል]] ምዕራፍ ፲፯፦ ቁጥር ፩ እስከ ፭ " ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ [[ቅዱስ ጴጥሮስ|ጴጥሮስ]]ንና [[ያዕቆብ (ሐዋርያ)|ያዕቆብ]]ን ወንድሙንም [[ቅዱስ ዮሐንስ|ዮሐንስ]]ን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ [[ሙሴ]]ና [[ኤልያስ]] ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ። እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።" </blockquote> ዓቢይ መሠረቱ ይሄ ሲሆን፣ በአገራችን የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት 'ቡሄ' የሚለውን ስያሜ አገኘች። ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት [[ስንዴ]] ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡ እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች [[ችቦ]] አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጡ፡፡ ታዲያ ያንን ማስታወሻ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች [[ሙልሙል ዳቦ]] የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የምናከብረውም ከዚህ በመነሣት ነው፡፡ == የቡሄ ዜማ == በዋዜማው የሠፈር ልጆች በየቤቱ እየዞሩ ሆያ ! ''አሲዮ ቤሌማ'' እያሉ ይጨፍራሉ። ቡሔ በሉ ቡሔ በሉ |2| ሆ ልጆች ሁሉ ሆ የኛማ ጌታ ሆ የአለም ፈጣሪ ሆ የሰላም አምላክ ሆ ትሁት መሀሪ ሆ በደብረታቦር ሆ የተገለፀው ሆ ፊቱ እንደፀሀይ ሆ በርቶ የታየው ሆ ልብሱ እንደ ብርሃን ሆ ያንፀባረቀው ሆ ...................... ድምፅህን ሰማና በብሩ ደመና |2| የቡሔው ብርሃን ለኛ በራልን |2| ………………….... ያዕቆብ ዩሃንስ ሆእንዲሁም ጴጥሮስ ሆ አምላክን አዩት ሆ ሙሴ ኤልያስ ሆ አባትም አለ ሆ ልጄን ስሙት ሆ ቃሌ ነውና ሆ የወለድኩት ሆ .......................... ታቦር አርሞንኤም ሆ ብርሃን የታየባቸው ሆ ከቅዱስ ተራራ ሆ ስምህ ደስ አላቸው ሆ ሰላም ሰላም ሆየታቦር ተራራ ሆ ብርሃነ መለኮት ሆ ባንቺ ላይ አበራሆ .......................... በተዋህዶ ሆ ወልድ የከበረው ሆ የእግዚአብሔር አብ ልጅ ወልደ ማርያም ነው ..................... ቡሔ በሉ ሆ ቡሔ በሉ ሆ የአዳም ልጆች ብርሃንን ተቀበሉ አባቴ ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ እናቴም ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ አጎቴም ቤት ሆ አለኝ ለከት ሆ አክስቴም ቤት አለኝ ለከት ሆ ተከምራል ሆ እንደ ኩበት ሆ ....................... የአመት ልምዳችን ሆ ከጥንት የመጣ ሆ የተከመረው ሆ ከመሶብ ይውጣ ሆ ከደብረ ታቦር ሆ ጌታ ስለመጣ ሆ የተጋገረው ሆ ሙልሙሉ ይውጣ ሆ ....................... ኢትዮጲያውያን ሆ ታሪክ አላችሁ ሆ ባህላችሁን ይዙ አጥብቃችሁ ሆ ችቦውን አብሩት ሆ እንደ አባቶቻችሁ ሆ ሚስጢር ስላለው ሆ ደስ ይበልስችሁ ሆ .................... አባቶቶቻችን ሆ ያወረሱን ሆ የቡሔን ትርጉም ሆ ያስተማሩን ሆ እንድንጠብቀው ሆ ለኛ የሰጡን ሆ ይህን ነውና ሆ ይስድረከቡን ሆ ........................ ለድንግል ማርያ ሆ አስራት የሆንሽ ሆ ቅዱሳን ጻድቃን ሆ የሙሉብሽ ሆ ሁሌም እንግዶች ሆ የሚያርፉብሽ ሆ .................. ለሐዋርያት ሆ የላከው መንፈስሆ ዛሬም ለኢትዮጵያ ሆ ፀጋውን ያፍስ ሆ በበጎ ምግባር ሆ እንድንታነፅ ሆ በቅን ልቦና ሆ በጥሩ መንፈስ ሆ በረከት ረድኤት ሆበሁላችን ይንፈስ በዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ ይሰጧቸውና እየገመጡ ጅራፋቸውን ሲያጮሁ ያመሻሉ። የቡሄ ዕለት ለእያንዳንዱ የቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ ልጅ አንዳንድ ሙልሙል ዳቦ በልጆቹ ልክ ይሰጣል። በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ ደግሞ ደብረ ታቦር ‘የተማሪዎች በዓል’ ነው። ተማሪዎቹ ቀደም ብለው “ስለ ደብረ ታቦር" እያሉ እህሉንም፣ ብቅሉንም፣ ጌሾውንም ይለምኑና ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምዕመናን ሁሉ ይጋብዛሉ። በአሁኑ ጊዜ፣ በተለይ በ[[አዲስ አበባ]] ይሄንን መንፈሳዊና ባህላዊ መሠረት በመልቀቅ ለሕሙማን፣ አዛውንት እንዲሁም ለእንስሳት ድንጋጤ የሚፈጥረውንና ለእሳት አደጋ የሚያጋልጠውን ባእዳዊ ርችት በመተኮስ ሆኗል የሚከበረው። ==ዋቢ ምንጮች== <references/> * የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ፣ “የበዓላትና ዓጽዋማት ቀኖና” ፤ http://ethiopianorthodox.org/amharic/abeyetbealat/yebealatenaatsewamat.pdf * http://eotc-mkidusan.org/site/index.php?option=com_content&task=view&id=331&Itemid=35 [[መደብ : የኢትዮጵያ በዓላት]] osn219ger4lgu3okvx2jk85ynfa5set ሸኮ 0 22408 394641 309077 2026-08-10T23:35:16Z Tamirateyayudashika 60051 /* ሕዝብ ቁጥር */ 5,000,000 394641 wikitext text/x-wiki ==ቋንቋ== ==ሕዝብ ቁጥር 5,000,000 == ==መልክዓ ምድር በተራራ የተከበበ አርንጓዴ ስፍራ == == ታሪክ በደቡብ ምዕራብ እትዮጵያ በሸኮ ፣ቴፒ፣ጉራፈርዳ ፣አይነዓምባ፣ዞዞ ፣ሞሪታ ወዘተ ይገኛል == ==ታዋቂ ፣ሰዎች ኮይናብ፣በዲያብ፣ጎታብ፣ቱድያብ፣እና 60 በላይ ጎሳዎች አሉዋቸው == {{መዋቅር-ብሔር}} ሸኮ የ[[ኢትዮጵያ]] ብሔር ነው። [[መደብ:የኢትዮጵያ ብሔሮች]] mt5e2dvqlhpq350i0b9g5cavvl3uq71 394642 394641 2026-08-10T23:36:08Z Tamirateyayudashika 60051 /* ቋንቋ */ 394642 wikitext text/x-wiki ==ቋንቋ ሸኮኛ== ==ሕዝብ ቁጥር 5,000,000 == ==መልክዓ ምድር በተራራ የተከበበ አርንጓዴ ስፍራ == == ታሪክ በደቡብ ምዕራብ እትዮጵያ በሸኮ ፣ቴፒ፣ጉራፈርዳ ፣አይነዓምባ፣ዞዞ ፣ሞሪታ ወዘተ ይገኛል == ==ታዋቂ ፣ሰዎች ኮይናብ፣በዲያብ፣ጎታብ፣ቱድያብ፣እና 60 በላይ ጎሳዎች አሉዋቸው == {{መዋቅር-ብሔር}} ሸኮ የ[[ኢትዮጵያ]] ብሔር ነው። [[መደብ:የኢትዮጵያ ብሔሮች]] eahix5l0b4nvj3vq5ktdl4mc8c8ggqo İstanbul Escort * Güncel Escort İstanbul * İstanbul Escort Bayan 0 55796 394626 2026-08-10T15:22:03Z ~2026-43939-90 60044 አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «VIP escort kalitesiyle '''İstanbul Escort''' dünyasında fark yaratıyoruz. Bağcılar, Üsküdar, Bakırköy başta olmak üzere 28 ilçede hizmet veren escort bayanlarımız, .<ref>sdww</ref>» 394626 wikitext text/x-wiki VIP escort kalitesiyle '''İstanbul Escort''' dünyasında fark yaratıyoruz. Bağcılar, Üsküdar, Bakırköy başta olmak üzere 28 ilçede hizmet veren escort bayanlarımız, .<ref>sdww</ref> 94btsw2ulitxb2y4q8omjhqclz48itx 394643 394626 2026-08-11T11:23:47Z ~2026-44072-38 60057 394643 wikitext text/x-wiki VIP escort kalitesiyle '''İstanbul Escort''' dünyasında fark yaratıyoruz. Bağcılar, Üsküdar, Bakırköy başta olmak üzere 28 ilçede hizmet veren escort bayanlarımız, .<ref>sdww</ref> [https://tr.techs.services/wiki/Anasayfa Google] at1sj99q8kqci60m328jb4dne9g8y80 İstanbul Escort - Güncel Escort İstanbul - İstanbul Escort Bayan 0 55797 394627 2026-08-10T15:23:24Z ~2026-43939-90 60044 አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «VIP escort kalitesiyle '''İstanbul Escort''' dünyasında fark yaratıyoruz. Bağcılar, Üsküdar, Bakırköy başta olmak üzere 28 ilçede hizmet veren escort bayanlarımız<ref>wdwdw</ref>» 394627 wikitext text/x-wiki VIP escort kalitesiyle '''İstanbul Escort''' dünyasında fark yaratıyoruz. Bağcılar, Üsküdar, Bakırköy başta olmak üzere 28 ilçede hizmet veren escort bayanlarımız<ref>wdwdw</ref> 3tvzkepjpqdtcaqwuklhiuv0t0hca7a