ፖድጎሪጻ
From Wikipedia
ፖድጎሪጻ (Подгорица) የሞንቴኔግሮ ዋና ከተማ ነው።
በ1995 ዓ.ም. በተደረገ ቆጠራ መሠረት የሕዝቡ ቁጥር 136,473 ነበር።
[ለማስተካከል] ስም
«ፖድጎሪጻ» ማለት «ከጎሪጻ ሥር» ማለት ነው። «ጎሪጻ» ማለት ደግሞ «ትንሽ ተራራ» ሲሆን ቅርብ የሆነ ኮረብታ ስም ነው።
በጥንትና በሮማ መንግሥት ዘመናት የቦታ ስም «ዶክሌያ» (Doclea) ነበር። የሮማ ንጉሥ ዲዮክሌትያን ከዚህ አገር ነበር። ስለዚህ ከሱ በኋላ የቦታ ስም «ድዮክሌያ» (Diocleia) ሆነ። በስላቮች ይህ ስም «ዱክልያ» (Дукля) ሆነ። በ12ኛው ምዕተ ዓመት «ሪብኒጻ» (Рибница) የተባለ አዲስ መንደር በዛ ተሠርቶ ከ1318 ዓ.ም. ጀምሮ «ፖድጎሪጻ» በሚለው ስም ታወቋል። ሆኖም ከተማው ከ1937 እስከ 1984 ዓ.ም. ድረስ «ቲቶግራድ» (Титоград) ተሰይሞ ነበር።