ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ

From Wikipedia

ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲኢትዮጵያ ፖለቲካ ወገን ነው። በኢንጂ. ሃይሉ ሻውል የሚመራ የኢትዮጵያ ህዝብ ፓርቲ ነው። ይህ ፓርቲ በግንቦት 7 ቀን 1997 ለሚካሄደው ምርጫ ተመሳሳይ አቋም ያላቸውን መኢአድን ኢዴአፓ-ማድህንን ኤዴሊንና ለዚሁ አላማ የተመሰረተውን ቀስተ ደመናን የሚያካትት ስብስብ ሆኖ የተመወረተ ነው። በ1997 ኣ.ም በተደረገው አገር አቀፍ ምርጫ ቅንጅት ከፍተኛ ውጤት በማምጣት (በአንዳንድ ውገኖችም አሸንፏል በመባል) ይታወቃል። የአዲስ አበባን አስተዳደር ማሸነፉም በተቀናቃኙ ፓርቲ በኢህአዴግ የታመነ ነው።

ይሁን እንጂ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት መሸነፉን ባለማመኑና ከምርጫ በኋላ የተደረጉት ድርድሮች ዘልቀው ባለመሄዳችው ከፍተኛ አለመረጋጋት ተፈጥሮ ቆይቶ መንግስት የቅንጅት መሪዎችን እንዲሁም ተቃውሞ ያስሙትን በዙ ውገኖችን በተለያዩ ክሶች ወንጅሎ በእስራት ይዞዋቸው ይገኛል። ሆኖም ጥቂት የቅንጅት አባሎች የፓርላማ ወንበራችውንም ተረክበው በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው።

በሌሎች ቋንቋዎች